ሐምሌ 17 2002 (JULY 24, 2010)
ክቡራትና ክቡራን፦
ፕሬዚደንት እንድሪያስ እሸቴን እና ዩኒቨርቲሲውን ባጠቃላይ ይህንን አንጋፋ አፍሪካዊ የትምህርት ማእከል እንደ ክቡር ተመራቂ እንድቀላቀል ስለሰጡኝ ክብር እና ልዩ ስጦታ ከልቤ ላመሰግን እወዳለሁ። ይህ ከኢትዮጵያ ጋር ልዩ ትስስር የሚሰጠኝ አዲስ ሁኔታ፣ በብዙ መንገድ ወደ እናት አገር ከመመለስ ጋር የሚተካከል ነው።
ግንቦት 15 2002 ዓ.ም
የተከበራችሁ ወዳጆቼ በመጀመሪያ እዚህ አርፍጄ በመገኘቴ ይቅርታ ልጠይቅ ይገባኛል። የኔ ጥፋት አይደለም። ። የኢትዮጵያን ህዝብ ገንዘብ መለስ ዜናዊ ለደላላ ኩባንያዎች እንዳሻው እያርከፈከፈ እንደሚያባክነው ብናውቅም ፣ እኔንም እንዲሁ በነዚሁ ደላላ ኩባንያዎች አማካኝነት ለመደለል ጥረት ሲያደርግ ቢከርምም ያሁኑን ጉዞዬን መቼም የኮንቲኔንታል አየር መንገድን ጉቦ ከፍሎ እዚህ ዘግይቶ እንዲደርስ እንዳላደረገው እጠረጥራለሁ። [...]