ምርጥ የእግር ኳስ ተጫዋቾች እና ምርጥ ቡድኖች እንዲኖሩን መንገድ እናመቻች፤ እንቅፋቶችን እናስወግድ

በደቡብ አፍሪቃ በመካሄድ ላይ ያለው የዓለም የእግር ኳስ ዋንጫ በአገራችን የእግር ኳስ መሠረታዊ ችግሮች ላይ እንድናተኩር እድል ሰጥቶናል። ኢትዮጵያ በወጣቶች የተገነባች እና ከፍተኛ የሆነ የእግር ኳስ ፍቅር ያለባት አገር ናት። በትላልቅ የእግር ኳስ ሜዳዎችና ግጥሚያዎች ኢትዮጵያዊያንንና የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ለማየት ግን አልታደልንም። አገራችን እንኳንስ በዓለም የእግር ኳስ ዋንጫ ልትወዳደር ቀርቶ ራሷ ካስጀመረችው የአፍሪካ እግር ኳስ ዋንጫ እንኳን ከተባረረች ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ ሆኗል። read more

ዘረኛውን አገዛዝ አስወግደን ፍትሃዊ እና ዴሞክራሲያዊ ስርአት የመንገንባት ሂደት ልንጀምር ይገባል

ወያኔ በተደጋጋሚ የብሔረሰቦችን መብት ስለማስከበሩ እንደሚያወራ ይታወቃል። እውነታው ግን፣ የብሔረሰቦች መብት ለወያኔ ዘረኛነቱን ለመሸፈን ከሚጠቀምባቸው ጭንብሎች አንዱ ከመሆኑ ባሻገር በተግባር ያሳየው ነገር አይደለም።

በመሰረቱ ዘረኛ የሆነና ከአንድ መንደር እና ቤተሰብ የመጡ ሰዎች በአገሪቱ ላይ የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ የበላይነት እንዲኖራቸው ተግቶ የሚሰራ ቡድን የብሔረሰቦችን መብት በእውነት ሊያስከብር አይችልም። ሊያደርጋቸው የሚችላቸው ብቸኛ ነገሮች ህዝቡን ለማታለል የተዘጋጁ read more

ዘረኛው አምባገነን መለስ ዜናዊ ወደ ካናዳ የሚያደርገው ጉዞ ከፍተኛ ተቃውሞ ገጠመው

ዘረኛው አምባገነን መለስ ዜናዊ በቡድን 20 ወይም ጂ20 ስብሰባ ለመሳተፍ ወደ ካናዳ የሚያደርገው ጉዞ ከፍተኛ ተቃውሞ ገጥሞታል።

በካናዳ የሚገኙ ሶማሊዎች ማህበር የሆነው “ካኔዲያን ሶማሊ ኮንግረስ” በዚህ ሳምንት ባወጣው መግለጫ ካናዳ መለስ ዜናዊን ለስብሰባው በመጋበዟ ማዘኑን ገልጿል። የመለስ ዜናዊ አገዛዝ በኢትዮጵያውያን እና በሶማሊዎች ላይ የሰብአዊ መብት ረገጣን የሚያደርግ፤ ዴሞክራሲያዊ ተቃዋሚ ፓርቲዎችን የሚጨቁን፤ read more

መድረክ ፓርቲ የምርጫ ቦርድን ውሳኔ በመቃወም ወደ ፍርድ ቤት ሄደ

የወያኔ ምርጫ ቦርድ የድጋሚ ምርጫ አይካሄድም በማለት ያስተላለፈውን ውሳኔ በመቃወም መድረክ ፓርቲ ለፍርድ ቤት አቤቱታ ማቅረቡ ታወቀ።

የፓርቲው ሊቀመንበር ዶ/ር በየነ ጴጥሮስ ለሬውተርስ የዜና አገልግሎት በሰጡት ቃል፤ 87 ገጽ ያለው የማስረጃ ሰነድ ለምርጫ ቦርድ ቢያቀርቡም፣ አንድም ማብራሪያ ወይም ምስክሮች እንዲያቀርቡ read more

ዘረኛውና አምባገነናዊው የወያኔ አገዛዝ ከግንቦት 15ቱ የምርጫ ተውኔት በኋላ በዜጎች ላይ የበቀል እርምጃ እየወሰደ መሆኑ ታወቀ

የምርጫ ተውኔቱ ከመካሄዱ በፊት ማስፈራራት ሲደርስባቸው በነበሩ ዜጎች ላይ የአገዛዙ ሎሌዎች የበቀል ጥቃት መፈጸም መጀመራቸውን ዘገባዎች እያሳዩ ነው።

ኢትዮሚድያ በሚባለው የዜና ድረ-ገጽ ላይ ሰሞኑን እየወጡ ያሉ ተከታታይ ዘገባዎች እንደሚያስረዱት፤ በተለይም በደቡብ ክልል በዜጎች ላይ በሰፊው ጥቃት እየደረሰ ነው። የምርጫ ታዛቢዎች በሃሰት እየተወነጀሉ እና ክስ ሳይመሰረትባቸው ለረዥም ቀናት ታስረው እንዲቆዩ እየተደረገ እንደሆነ ታውቋል። read more

የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን ስርጭት እንደገና ተቋረጠ፤ የወያኔ አገዛዝ ለአፈናው ተጠያቂ ነው ተባለ

ዘረኛውና አምባገነናዊው የወያኔ አገዛዝ የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን ወይም ኢሳትን አፍኗል ተባለ። ኢሳት ቅዳሜ እለት ባስተላለፈው ዘገባ፣ የጣቢያው ማኔጅመንት የወያኔ አገዛዝ የቴሌቭዥን ድርጅቱን ስለማፈኑ ማስረጃ ለማሰባሰብ ችሏል ብሏል።

የሳተላይት አገልግሎት አቅራቢ ኩባንያው በበኩሉ የአፈናውን ምንጭ ለመረዳት ምርመራውን እንደቀጠለ እና በቂ ማስረጃ ሲያገኝም ህጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ መግለጹን የኢሳት መግለጫዎች አሳይተዋል። read more

ዘረኛውና አምባገነናዊው የወያኔ አገዛዝ በኦጋዴን ንጹሃን ዜጎችን እየገደለ መሆኑ ተዘገበ

የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃነት ግንባር (ኦብነግ) የወያኔ አገዛዝ ባለፈው ወር ብቻ በኦጋዴን 71 ንጹሃን ዜጎችን መግደሉን ለዜና አውታሮች በላከው መግለጫ አስታውቋል።

ግንባሩ በመግለጫው፥ ወንዶች ቤተሰቦቻቸው ፊት ሲገደሉ፤ ሴቶች ተደብድበዋል፣ ተደፍረዋል፣ ተገድለውማል ማለቱን ሬውተርስ የዜና አውታር ዘግቧል። ጉዳዩን አስመልክቶ የተጠየቀው የበረከት ስምኦን ምክትል ሽመልስ ከማል አገዛዙ ጉዳዩን እየመረመረ እንደሚገኝ እና እስካሁን የተደረገው ምርመራ መሰረተ ቢስ read more

በኢትዮጵያ ላለው ከፍተኛ የዋጋ ግሽበት የወያኔ የገንዘብ ፖሊሲ ተጠያቂ ነው ተባለ

በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንን ለባሰ ድህነት የዳረገው የዋጋ ግሽበት ወያኔ እንደሚለው እድገት የፈጠረው ሳይሆን በአገዛዙ የገንዘብ ፖሊሲ ምክንያት የተፈጠረ ነው ተባለ።

ባለፉት አራት አመታት በኢትዮጵያ ከቁጥጥር ውጪ በወጣ መልኩ ከሚታየው የዋጋ ግሽበት የተነሳ አብዛኞቹ ኢትዮጵያውያን መሰረታዊ ፍላጎቶቻቸውን ማሟላት እያቃታቸው የኑሮ ደረጃቸው ወደከፋ ደረጃ ማሽቆልቆሉ እና read more

የወያኔ ጦር የወታደሮች ፍልሰት ችግር እንዳለበት ታወቀ

የወያኔ ጦር ከፍተኛ የሆነ የወታደሮች ፍልሰት ችግር እንዳለበት የግንቦት 7 ድምጽ ሪፖርተር ከኢትዮጵያ በላከው ዘገባ አስታውቋል።

ዘጋቢው ከሰሜን ኢትዮጵያ ባስተላለፈው መረጃ፣ በሰሜን ምእራብ ኢትዮጵያ በጠገዴ ወረዳ በተለያዩ ቀበሌዎች ተሰማርቶ የነበረው የ4ኛ ሻለቃ ልዩ ሃይል በደረሰበት የወታደሮች ፍልሰት በመዳከሙ አገዛዙ በአዲስ ምሩቆች ሊሞላው ተገዷል። አብዛኞቹ ወታደሮች በክህደት እንደሚለቁ የታወቀ ሲሆን፤ read more

በቅርቡ በኬንያ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ የተሾመች ግለሰብ የወያኔ ዘረኛ ፖሊሲ ተጠቃሚ ነች ተባለ

በኬንያ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ የኢሚግሬሽን ካውንስለር ሆና በቅርቡ የተመደበችው ግለሰብ ለስራው የሚያስፈልገውን ብቃት የሌላት እና የወያኔ አገዛዝ ዘረኛ ፖሊሲ ተጠቃሚ ነች ሲሉ የኤምባሲው ምንጮች ስሞታ አሰምተዋል።

ለግንቦት 7 ድምጽ ከስፍራው የደረሰው መረጃ እንደሚያመለክተው፣ አለም ተክሉ የተባለችው ግለሰብ የወያኔ የቀድሞ ታጋይ ስትሆን፣ የተማረችው እስከ ሶስተኛ ክፍል ድረስ ብቻ ነው። ኤምባሲው read more

ፍሪደም ሃውስ የተባለው ተቋም የወያኔ አገዛዝ የዘር አድሎ ይፈጽማል፤ በኢትዮጵያ ያለው አፈናም ከቀደመው አመት የከፋ ሆኗል አለ

ፍሬደም ሃውስ የተባለው አንጋፋ አለም አቀፍ የነፃነት ተሟጋች ድርጅት ሰሞኑን ባወጣው አመታዊ ሪፖርት የወያኔ አገዛዝ የዘር አድሎን በሰፊው እንደሚፈጽም፤ እንዲሁም የኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሁኔታ ከቀደመው አመት የከፋ መሆኑን ገልጿል።

ተቋሙ የወያኔ አገዛዝ በኢኮኖሚ እና በፖለቲካ ጉዳዮች ላይ የዘር አድሎ እንደሚፈጽም እና ከትግራይ ለሆኑ ሰዎች እንደሚያደላ ተናግሯል። በሌሎች ብሔረሰቦች ላይም በሰፊው አድሎ እንደሚፈጸም መስክሯል። read more

የኢትዮጵያ ህዝብ ሞትን ፈርቶ ለጨቋኞች እና ለዘራፊዎች አይንበረከክም

ከግንቦት 7 የፍትህ የነጻነትና የዴሞክራሲ ንቅናቄ

የኢትዮጵያ ህዝብ ለመብቱና ለነፃነቱ ሲታገሉ በባዕዳን ፋሺስቶችና ዬኔ ብሎ በሚላቸዉ ጨካኝ ልጆቹ የተጨፈጨፉ አያሌ ሰማዕታት ልጆች አሉት። በ1928 ዓም በወርሃ ዬካቲት የፋሺስት ኢጣሊያ ወታደሮች ሽማግሌ ከህፃንና ጎበዝ ከደካማ ሳይለዩ በሕይወት ቆሞ ሲሄድ ያዪትን ኢትዮጵያዊ ሁሉ በጭካኔ በመግደል በአንድ ጀምበር ከ30ሺ በላይ ኢትዮጵያዉያንን ጨፍጭፈዋል። በ1969 ዓም እና በ1997 ዓም ደግሞ ኢትዮጵያን read more

የተከበሩ ወ/ሮ አና ጎምዝ በዋሽንግተን ዲስ ለኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቭዝን በተደረ የገንዘብ ማሰባሰብ ዝግጅት ያደረጉት ንግግር

ግንቦት 15 2002 ዓ.ም

የተከበራችሁ ወዳጆቼ በመጀመሪያ እዚህ አርፍጄ በመገኘቴ ይቅርታ ልጠይቅ ይገባኛል። የኔ ጥፋት አይደለም። ። የኢትዮጵያን ህዝብ ገንዘብ መለስ ዜናዊ ለደላላ ኩባንያዎች እንዳሻው እያርከፈከፈ እንደሚያባክነው ብናውቅም ፣ እኔንም እንዲሁ በነዚሁ ደላላ ኩባንያዎች አማካኝነት ለመደለል ጥረት ሲያደርግ ቢከርምም ያሁኑን ጉዞዬን መቼም የኮንቲኔንታል አየር መንገድን ጉቦ ከፍሎ እዚህ ዘግይቶ እንዲደርስ እንዳላደረገው እጠረጥራለሁ። የሞከረም አይመስለኝም። read more

ለኢትዮጵያ የሚድያ አውታሮች በሙሉ

ለኢትዮጵያ የሚድያ አውታሮች በሙሉ

ከግንቦት 7 የፍትህ የነጻነትና የዴሞክራሲ ንቅናቄ ጽ/ቤት

የሰኔ 1 1997 ዓ.ም የዴሞክራሲ ስማእታትን በሚመለክት የተላለፈ መልእክት

ሰኔ 1 2002 ዓ.ም

ዛሬ ሰኔ 1 ቀን ነው:: የዛሬ 5 አመት በእዚህ እለት በምርጫ የሰጠነው ድምጻችን ይከበር በማለት በሰላማዊ መንገድ ጥያቄ ለማቅርብ በወጡ የሃገሬው ዜጎቸ ላይ የመለስ ዜናዊ አምባገነናዊ አገዛዘ በወሰደው አረመኒያዊ የእመቃ እርምጃ ከ40 በላይ የሚሆኑት ህይወታቸው አልፏል። በሽህ የሚቆጠሩ ዜጎችም አሰቃቂ ቅጥቀጣና የወህኒ እጎራ ተፈጽሞባቸዋል። read more

ሽምግልና ተዋረደ!!!

ሽምግልና ተዋረደ!!! ራሳቸውን “የሃገር ሽማግሌ” ብለው በሚጠሩ የመለስ ዜናዊ ተላላኪዎች ምክንያት ሽምግልና ረከሰ!!! ሽምግልና በደልን ማርዘሚያ ሆነ!!!

ሽምግልና አያት፣ ቅድመ-አያቶቻችን አዳብረው ያቆዩልን እጅግ የተከበረ ማኅበራዊ ተቋም ነው። ሽምግልና ተደጋግፎ ለመኖር፤ ግጭቶችን ለመቀነስ እና ፍቅርን ለማብዛት ማኅበረሰባችን በብዙ ምዕተ ዓመታት ልምድ ያዳበረውና ሞገስን የቸረው በየጊዜውም እያሻሻለው የሚሄድ ማኅበራዊ እሴት ነው። read more

Page 10 of 22« First...«89101112»20...Last »
© 2008-2009