ዘረኛው የወያኔ አገዛዝ ቁንጮ የሆነው መለስ ዜናዊ ለአገር ውስጥ ጋዜጠኞች በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ፡ ህገመንግሥቱን ተቀብለው በሰላማዊ መንገድ መንቀሳቀስ እስከ ተስማሙ ድረስ ከማንኛውም ሃይል ጋር ለመደራደር እንደሚፈልግ ገልጾ በሃይል ከስልጣን ሊያባሪሩኝ ነው እያለ ዘወትር ከሚከሳቸው የግንቦት7 እና የ ኦሮሞ ነጻነት ግንባር ጋርም read more
ዘረኛውና አምባገነናዊው የወያኔ አገዛዝ በጠረፋማ ክልሎች ሊዘረጋ ያቀደው አዲስ የቁጥጥር መዋቅር በአካባቢዎቹ የሚመላለሱ የትጥቅ ቡድኖችን እንቅስቃሴ ለመግታት ያለመ እንደሆነ ለዝግጅት ክፍላችን የደረሰ ዘገባ አሳይቷል።
አገዛዙ በአራት የጠረፍ ክልሎች “የገበሬ መንደር” የሚባል እና ከቀበሌ ያነሰ የቁጥጥር መዋቅር ለመመስረት መነሳቱን ሐሙስ እለት መዘገባችን ይታወሳል። ይህንንም እቅድ ለማስፈጸም፣ read more
ባመጧቸው ጥሩ ውጤቶች የተመለመሉ የመጀመሪያ ዲግሪ ምሩቃን በአዳማ እና በመቀሌ ዩኒቨርሲቲዎች ተሰብስበው ስለ አብዮታዊ ዴሞክራሲ ሲሰበኩ እንደሰነበቱ መጥቀሳችን ይታወሳል።
የግንቦት 7 ድምጽ የአዲስ አበባ ሪፖርተር አጠናቅሮ በላከው ተከታይ ዘገባ እንዳስታወቀው፥ በስልጠናው ፍፃሜ ላይ በሁለቱ የስልጠና ቦታዎች መቶ መቶ ተማሪዎች ለሁለተኛ ዲግሪያቸው read more
ወያኔ በኢትዮጵያ አስገኝቻለሁ የሚለው የደብል-ዲጂት የኢኮኖሚ እድገት ከኢትዮጵያውያን አልፎ በአንዳንድ የአለማቀፍ የመረጃ አውታሮች ዘንድ ጥያቄ ማስነሳት መጀመሩ እየተስተዋለ ነው።
ፋይናንሻል ታይምስ የተባለው ታዋቂ ጋዜጣ ሰሞኑን ያወጣው ጽሁፍ፣ በኢትዮጵያ አለ የሚባለው እና አንዳንድ የአለማቀፍ ባለሙያዎች የሚቀበሉት የኢኮኖሚ እድገት ወሬ ምንጩ በውል read more
የወያኔ ዘረኝነት፣ ትምክህት እና የስሌት ስህተት እርስበርስ የሚመጋገቡ ናቸው። ትዕቢቱ “ስህተቱን” ግዙፍ ሲያደርገው፤ ዘረኝነቱ ደግሞ “ስህተቱን” አስነዋሪና አሳፋሪ ያደርገዋል። በዘረኝነትና ትዕቢት ከተነዱ በርካታ ስህተቶች አንዳንዱን ለአብነት ያህል እናንሳ።
ዘረኛውና አምባገነናዊው የወያኔ አገዛዝ ከትግራይ ብሔረሰብ ተመልምለው ከአንድ አመት በላይ የስለላ ሙያ ስልጠና ሲሰጣቸው የቆዩ ወጣቶችን በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች በሚገኙ ወረዳዎች በአማካሪነት ስም እየመደበ መሆኑን የግንቦት 7 ድምጽ ሪፖርተር ከሰሜን ኢትዮጵያ ባስተላለፈው ዘገባ አስታውቋል። read more
የወያኔ አገዛዝ ኢትዮጵያውያን በሙሉ አብዮታዊ ዴሞክራሲን እንዲቀበሉ ለማድረግ ባለው እቅድ ሰሞኑን መቀሌና አዳማ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ በግዴታ የአብዮታዊ ዲሞክራሲ ስልጠና እንዲወስዱ የተደረጉት የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ሰቃዮች ስልጠናቸውን አጠናቀዋል። ስልጠናውን ከተከታተሉት ውስጥ 200 የሚሆኑት read more
የወያኔ አገዛዝ ባለፉት በርካታ አመታት በአንዳንድ የኦሮሚያ እና የደቡብ ክልሎች አካባቢዎች በስራ ላይ ያዋላቸውን ከቀበሌ ያነሱ የቁጥጥር መዋቅሮች ወደ አፋር፣ ሶማሌ፣ ጋምቤላ እና ቤኒሻንጉል ክልሎች ለማስፋፋት በዝግጅት ላይ መሆኑ ታውቋል።
የግንቦት 7 ድምጽ ዘጋቢ ከኢትዮጵያ አጠናቅሮ በላከው ዘገባ መሰረት፥ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አዲሱ ለገሰ የሚመራ ቡድን በነዚህ ክልሎች “የገበሬ መንደር” read more
የወያኔ አገዛዝ በግንቦት 15ቱ የምርጫ ተውኔት መቶ በመቶ መርጦኛል ያለውን ህዝብ መልሶ ስለምርጫው ትክክለኛነት ለማሳመን ዘመቻ መጀመሩን የግንቦት 7 ድምጽ ሪፖርተር ከአዲስ አበባ ባስተላለፈው ዘገባ አስረድቷል።
በወያኔ ቁጥጥር ስር በሚገኙ የህዝብ መገናኛ ብዙሃን ተቀጥረው የሚሰሩ ልማታዊ ጋዜጠኛ ተብዬዎች በተለያዩ ክልሎች የውይይት መድረኮችን በማዘጋጀት ወያኔ የፓርላማውን መቀመጫ read more
በወልቃይት ጠገዴ ኢትዮጵያውያን ላይ የሚደርሰውን ግፍ ለማስቆም የኢትዮጵያውያን የትብብር ትግል አስፈላጊ ነው ሲሉ ልሳነ-ግፉአን የተባለ የሰብአዊ መብት ተከራካሪ ድርጅት ምክትል ሊቀመንበር ገልጸዋል።
አቶ አባይ መንግስቱ ለግንቦት 7 ድምጽ ሬድዮ በሰጡት ቃለ-መጠይቅ፥ ዘረኛውና አምባገነናዊው የወያኔ አገዛዝ ወልቃይት ጠገዴን ከተቆጣጠረ ወዲህ በአካባቢው ነባር ነዋሪ read more
የወያኔው የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስትር ሱፊያን አህመድ፥ “ኢትዮጵያ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ በአለም ፊት በተመጽዋችነት ስሟ አይነሳም” ማለቱ የወያኔው አገዛዝ ከዚህ ቀደም የገባቸውን ተመሳሳይ ቃላት እንዳስታወሳቸው የፖለቲካ ተንታኞች ገልጸዋል።
የቀድሞው የወያኔ ታጋይ አማረ አረጋዊ ንብረት የሆነው read more
ከወያኔ ዋና ባለስልጣናት አንዱ የሆነው ስብሃት ነጋ ከአንድ የቻይና ኩባንያ በደላላነት ስም የመቶ ሃምሳ ሚሊዮን ዶላር ጉቦ ተቀብሏል ሲል አንድ አዲስ መጽሃፍ ወንጅሏል።
አዲስ ቮይስ የተባለው የመረጃ ድረ-ገጽ የገመገመው እና ዶ/ር አክሎግ ቢራራ በተባሉ read more
በዋሽንግተን ዲሲ እና አካባቢው የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ሐሙስ ሐምሌ 29 ቀን 2002 ዓም በቻይና ኤምባሲ ፊት ለፊት በመገኘት አገሪቱ ለዘረኛውና አምባገነናዊው የወያኔ አገዛዝ የምታደርገውን ድጋፍ በመቃወም ሰልፍ አድርገዋል።
ሰልፈኞቹ፥ የወያኔ አገዛዝ የኢትዮጵያ ህዝብ መረጃ እንዳያገኝ ለሚያደርገው እገዳ ቻይና የምትሰጠውን ድጋፍ እንድታቆም ጠይቀዋል። አገዛዙ የአሜሪካ ድምጽ ሬድዮን፣ የጀርመን ድምጽ ራድዮን፣ read more
የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ከ4.1 ቢሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ ስድስት የመንገድ ስራ ፕሮጀክቶችን ለአምስት ኩባንያዎች ሰጥቶ ስምምነት መፈራረሙን ሪፖርተር የተባለውና ከገዢው ፓርቲ ጋር ትስስር ያለው ጋዜጣ ዘግቧል።
ኩባንያዎቹም፥ መከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ፣ ሱር ኮንስትራክሽን፣ እንይ ኮንስትራክሽን፣ ኢትዮ-ጀነራል ኮንስትራክሽን እና ማክሮ ኮንስትራክሽን መሆናቸው ታውቋል። read more
በአዲስ አበባ ከተማ የትናንሽ ንግድ ባለቤቶች ግብር በዝቶብናል በማለት ስሞታ እያሰሙ እንደሆነ ከስፍራው የደረሰን ዘገባ አሳይቷል።
የግንቦት 7 ድምጽ ዘጋቢ ተዘዋውሮ ያናገራቸው ግለሰቦች የተጫነባቸው መጠን ከአቅማቸው በላይ እንደሆነና መክፈል ተስኗቸው እስር ቤት እንሄዳለን ብለው እንደሚጠብቁ ገልጸዋል። ግለሰቦቹ፥ ለመጣጣር እና ልጆቻቸውን ለማዳን ሲሉ መንግስት ለጥቃቅን እና መለስተኛ ንግዶች የሚሰጠውን ብድር በመውሰድ read more