የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥንን (ኢሳት) በሚመለከት ሰሞኑ አዲስ አበባን ያዳረሰው ጭውውት የሚከተለውን ይመስላል።
“ዳዊት ጎልያድን ገደለ!”
“በምን?”
“በወንጭፍ!”
“ኢሳት ኢቲቪን ከሳተላይት አወረደ !”
“በምን?”
“ገና ባልታየው ችሎታው”
ይህ ጭውውት እንደ እረኛ ዘፈን ምስጢሮችንና ሕዝባዊ መልዕክቶችን ይዟል። read more
ሐምሌ 17 2002 (JULY 24, 2010)
ክቡራትና ክቡራን፦
ፕሬዚደንት እንድሪያስ እሸቴን እና ዩኒቨርቲሲውን ባጠቃላይ ይህንን አንጋፋ አፍሪካዊ የትምህርት ማእከል እንደ ክቡር ተመራቂ እንድቀላቀል ስለሰጡኝ ክብር እና ልዩ ስጦታ ከልቤ ላመሰግን እወዳለሁ። ይህ ከኢትዮጵያ ጋር ልዩ ትስስር የሚሰጠኝ አዲስ ሁኔታ፣ በብዙ መንገድ ወደ እናት አገር ከመመለስ ጋር የሚተካከል ነው። read more
በሆላንድ ዋና ከተማ አስምተርዳም በኢትዮጵያውያን ስደተኞች በተዘጋጀ በአል ላይ የወያኔ ቅጥረኞች ሁከት ለመፍጠር ያደረጉት ሙከራ በዝግጅቱ ታዳሚዎች እንደከሸፈ ለዝግጅት ክፍላችን ከስፍራው የደረሰ ዘገባ አሳይቷል።
ከሐምሌ 22 እስከ ሐምሌ 24 በአምስተርዳም የተካሄደው 8ኛው አመታዊ የኢትዮጵያዊያን-አውሮፓውያን የስፖርትና የባህል ፌስቲቫል በብዙ ሽህ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንና አውሮጳውያን በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ ተከብሮ ውሏል። read more
የወያኔ አገዛዝ ኢትዮጵያውያን በሙሉ አብዮታዊ ዴሞክራሲን እንዲቀበሉ ለማድረግ ባለው እቅድ መሰረት ሰሞኑን የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ሰቃዮችን ያለ ፈቃዳቸው ሲሰብክ መቆየቱ ታውቋል።
አገዛዙ ኢትዮጵያውያን በሙሉ በአብዮታዊ ዴሞክራሲ ላይ የተመሰረ አንድ አመለካከት እንዲኖራቸው እና ተቃውሞ እንዲያቆሙ የማድረግ እቅድ እንዳለው read more
የወያኔ አገዛዝ ባለፉት አስር አመታት ውስጥ የአገሪቱን የደን ሽፋን በሶስት እጥፍ ጨምሬያለሁ በማለት ያወጣውን ሪፖርት የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ባለሙያዎች “እውነትነት የጎደለው እና ጨቅላ” እንዳሉት አፍሪክጄት የተባለ የዜና ድረ-ገጽ ዘግቧል።
በወያኔ ቁጥጥር ስር የሚገኘው የግብርና ሚኒስቴር በዚህ ወር ባወጣው read more
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአለም ላይ በከፍተኛ ደረጃ ትርፋማ ከሆኑ አየር መንገዶች አንዱ ነው በተባለ ማግስት አንዳንድ የተቋሙ ሰራተኞች በወደፊት እጣው ላይ ጥያቄ እያነሱ ነው።
ናዝሬት ዳት ካም የተባለው የመረጃ ድረ-ገጽ “ኤር ትራንስፖርት ወርልድ” የሚባለውን ጋዜጣ ጠቅሶ እንደዘገበው፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከአለም 16ኛ፣ ከአፍሪካ ደግሞ 1ኛው read more
በ2000 አመተ ምህረቱ ህገ-ወጥ የማሟያ ምርጫ ተመርጠዋል በሚል በአዲስ የተለያዩ የቀበሌና የወረዳ አስተዳደራዊ መቀመጫዎችን የተረከቡ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ያለ ምርጫ በተሰበሰቡ አዳዲስ ሹመኞች እየተተኩ መሆኑን ከአዲስ አበባ የደረሰን ዘገባ አስታውቋል። read more
የተሻለ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታ ፍለጋ ወደ ውጭ በሚሰደዱ ኢትዮጵያውያን ላይ የሚደርሰው እንግልት ቀጥሎ በዚህ ሳምንት በደቡብ አፍሪካ ሶስት ኢትዮጵያውያን በጩቤ ተወግተው መጎዳታቸው ተዘግቧል።
“ፍሮም ዘ ኦልድ” የተባለ የደቡብ አፍሪካ የዜና ድረ-ገጽ እንደዘገበው፣ የሶስቱ ኢትዮጵያውያን መኪናዎች በቁጣ በተሰባሰቡ የአገሬው ሰዎች ከተሰባበሩ በኋላ read more
ቅዳሜ ሃምሌ 24 ቀን 2002 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ በደረሰ የመኪና አደጋ ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ ሃያ ስድስት ሰዎች ሞተው በርካቶች መቁሰላቸው ተዘግቧል።
በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፣ በተለምዶ 18ኛው ማዞሪያ ተብሎ read more
የቀደሞው የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚደንት እና እውቁ የጸረ-ዘረኛነት የነጻነት ታጋይ ታቦ ኢምቤኪ ባለፈው ሳምንት ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የክብር ዶክተሬት በተቀበሉበት ክብረ በአል ላይ ያደረጉት ንግግር አነጋጋሪ ሆኖ ሰንብቷል።
ባለፈው ቅዳሜ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ባዘጋጀው የተማሪዎች ማስመረቂያ በአል ላይ በመገኘት የክብር ዶክተሬት ዲግሪያቸውን የተቀበሉት ፕሬዚደንት ኢምቤኪ ያደረጉት read more
አሜሪካ ከዚህ በኋላ በሙስና በተዘፈቁ መሪዎቻቸው አማካኝነት ከአፍሪካውያን ለተሰረቀ ገንዘብ ማከማቻነት አታገለግልም ሲሉ የኦባማ አስተዳደር የፍትህ ቢሮ ሃላፊ አቶ ኤሪክ ሆልደር መናገራቸውን የዩጋንዳው ደይሊ ሞኒተር ዘግቧል።
ባለፈው ሳምንት በዩጋንዳ በተካሄደው የአፍሪካ አንድነት ጉባኤ ላይ ለአገራቱ መሪዎች ራሳቸው ባደረጉት ንግግር፣ የአሜሪካ መንግስት ከአፍሪካ ተሰርቆ በምእራባውያን read more
በአዲስ አበባ ቂርቆስ ክፍለ ከተማ ለከተማ ልማት በሚል እንደሚፈናቀሉ የተነገራቸው በርካታ ነዋሪዎች ያለመድረሻ እንደቀሩ ለግንቦት 7 ድምጽ የአዲስ አበባ ዘጋቢ ስሞታቸውን ገልጸዋል።
215 የሚሆኑት ዜጎች የሚፈናቀሉበት ምክንያት መኖሪያዎቻቸው ባሉበት ቦታ ኮንዶሚኒየሞች እንዲሰሩ ስለታቀደ ነው። ምንም እንኳ በወያኔ ቁጥጥር ስር ያሉ መገናኛ ብዙሃን ተፈናቃዮቹ ከፍተኛ ካሳ እንደተሰጣቸው ቢናገሩም፣ ከዚህ ቀደም ከልደታ አካባቢ የተፈናቀሉ read more
ትምህርት የእውቀት አድማስን ካላሰፋ፤ አዳዲስ ክህሎቶችን ካላሳወቀ፤ የእለት ከእለት ኑሮን ካላሻሻለ እና አዎንታዊ የባህርይ ለውጥ ካላመጣ ፋይዳው እምን ላይ ነው?
የወያኔ የትምህርት ሥርዓት ከላይ ከዘረዘርናቸው ውስጥ ለአንዱም የተዘጋጀ አይደለም። ወያኔ ትምህርት ቤቶችንና ዩኒቨርስቲዎችን ከእውቀትን መገበያያነት ይልቅ እጅግ ኋላቀር የሆነ ዘረኛና ጎጠኛ አስተሳሰብ ማራቢያና ማሰራጫ ተቋማት አድርጎዓቸዋል። read more
የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን ድርጅት (ኢሳት) በዚህ ሳምንት እንደገና መታፈኑን እና ስርጭቱ መቋረጡን ድርጅቱ በለቀቀው መግለጫ አስታወቀ።
መግለጫው አፈናውን የሚያኬሄደው ዘረኛውና አምባገነናዊው የወያኔ አገዛዝ ስለመሆኑም ድርጅቱ ማስረጃ እንዳለው ገልጿል። አገዛዙ ኢሳት ቴሌቪዥንን ለማፈን በሚያካሄደው read more
አዲስ አበባን ጨምሮ በበርካታ የአገሪቱ ክፍላት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና የንግድ ድርጅቶቻቸው በኤሌክትሪክ ሃይል እጦት ምክንያት እየተንገላቱ ባሉበት ወቅት የወያኔ አገዛዝ የኤሌክትሪክ ሃይል ለጎረቤት አገሮች ለመሸጥ ዝግጅቶች አጠናቅቄያለሁ ማለቱ ተዘግቧል። read more