ዘረኛዉ የወያኔ አገዛዝ ካድሬዎቹን በየቀበሌዉ እየላከ የአዲስ አበባን ነዋሪዎች ለምርጫ ካልተመዘገባችሁ እያለ ቢያስፈራራም በመጪው ሚያዚያ ወር ለሚካሄደው የአዲስ አበባና የወረዳ ምርጫዎች የተመዘገበው መራጭ ቁጥር ከተጠበቀው በታች በመውረዱ ወያኔ ከክልል ከተሞች የራሱን ደጋፊዎች በማስመጣት በምርጫው እንዲሳተፉ ዛሬ ስልጠና መስጠት መጀመሩን የግንቦት ሰባት ምንጮች ከአዲሰ አበባ በላኩልን ዜና ገለጹ። ከተለያዩ ክልሎች የመጡ የወያኔ ደጋፊዎች አዲስ አበባ ዉስጥ [...]
ማስረሻ መኮንን ነኝ ከቃሊቲ እንደምን ሰነበታችሁ ግንቦቶች - እቺ ደብዳቤዬ እንደምትደርሳችሁ አልጠረጠርም፤ ካልደረሰችም እርግጠኛ ነኝ እናንተዉ ፈልጋችሁ ታገኟታላችሁ። ለመሆኑ እንደምን ከረማችሁ? ዘረኞቹ የወያኔ ካድሬዎች በዚያ ሰሞን ዉጭ አገር ካሉ ሽብርተኞች ጋር ትገናኛለህ ብለዉ ዘብጥያ ወርዉረዉኝ ይሄዉና ሳላናግራችሁ ሳታናግሩኝ ድፍን አንድ አመት አለፈን። መቼም የማይለመድ ነገር የለም መታሰርም ኑሮ ሆኖ ይሄዉና እስር ቤቱን ለመድኩት። ደሞስ የወያኔ [...]
ቀደም ብሎ ከቤሻንጉል ጉምዝ የተፈናቀሉ አማራዎች፣ የደረሰባቸው እልቂትና እንግልት ሳያንሳቸው አሁን ደግሞ የመንግስት ባለስልጣናት እያስፈራሩዋቸውና እያዋከቧቸው መሆኑን ተፈናቃዮችን ያነጋገረው ዘጋቢያችን በላከልን ሪፖርት ገለጸ። እንደዘጋቢያችን ሪፖርት ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ተፈናቅለው በምእራብ ጎጃም ዞን በፍኖተሰላም ከተማ ሜዳ ላይ ወድቀው የሚገኙት አማራ ተወላጅ አርሶደአሮች ከክልሉ ዋና ከተማ እና ከዞኑ የተውጣጡ የወያኔ ሆድ አደር ባለስልጣናት ትናንት ሰብስበው ያነጋገሩዋቸው ቢሆንም ፣ [...]
ካለፈዉ አመት አጋማሽ ጀምሮ ኢትዮጵያ ዉስጥ በከፍተኛ ፍጥነት እያሽቆለቆለ የመጣዉ የዉጭ ምንዛሬ ክምችት በፈጠረዉ ችግር የተነሳ የንግዱ ህብረተሰብና የወያኔ አገዛዝ ታይቶ የማይታወቅ ጭቅጭቅ ዉስጥ መግባታቸዉን አንድ በቅርቡ ንብረታቸዉን ሽጠዉ ወደ አዉሮፓ የመጡ ኢትዮጵአዊ ነጋዴ ተናገሩ። እኚህ ላለፉት 17 አመታት በዉጭ ንግድ ስራ ላይ ተሰማርተዉ የነበሩ አቶ አሀዱ ወሰንየለህ የተባሉ ነጋዴ እንደተናገሩት በአገሪቱ ውስጥ የተፈጠረውን ከፍተኛ [...]
በደቡብ አፍሪቃ የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ዘረኛው የወያኔ አገዛዝ ለአባይ ግድብ መዋጮ በሚል የጠራውን ስብሰባ እንዲያቆምና ተሰብሳቢዎችም እንዲበተኑ ያደረጉ ሲሆን ኢትዮጵያውያኑ ይህን እርምጃ ለመውሰድ የተነሳሱት የወያኔን አገዛዝ ቅጥ ያጣ ፖሊሲ በመቃወም መሆኑን ዘጋቢያችን ከስፍራው ባስተላለፈልን ሪፖርት አመለከተ። ዘጋቢያችን እንደገለጠው ኢትዮጵያኑ የወያኔ አገዛዝ ባለስልጣናት በድብቅ ስብሰባ የማዘጋጀታቸውን መረጃ እንዳገኙ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተሰባስበው በመቃማቸው የወያኔ ባለስልጣናት ስብሰባውን በመሰረዝ [...]
አማራን ካላጠፉ እንቅልፍ ባይናቸዉ አልዞር ያለዉ የወያኔ ዘረኞች ያፈናቀሏቸዉን ስልሳ የአማራ ተወላጆች ይዞ ይጓዝ የነበረ የጭነት መኪና ተገልብጦ ሃምሳ ዘጠኙ መሞታቸዉን ተፈናቃይ የአማራ ወገኖቻችንን እየዞረ ያናገረዉ የግንቦት ሰባት ዘጋቢ በላከልን ዜና ገለጸ። ይህንን ያክል ብዛት ያለዉን ተሳፋሪ ህይወት የቀጠፈ አሰቃቂ አደጋ የደረሰዉ 60 ተፈናቃዮችን አሳፍሮ ይጓዝ የነበረዉ አይሱዙ መኪና ትክሻ በሚባል አካባቢ ጀዴሳ ወንዝ ውስጥ [...]
በግፈኛውና ዘረኛው የወያኔ አገዛዝ በቃሊቲ እስር ቤት የሚገኙት ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋና አቶ አንዱአለም አራጌን ፍርድ ቤት ሳያቀርቡ መቅረታቸውን ዘጋቢያችን ከአዲስ አበባ ባስተላለፈልን ሪፖርት ገለጸ። የወያኔው አሻንጉሊት ፍርድ ቤት በ አቶ አንዱ አለም አራጌ የክስ መዝገብ በፌደራል ከፍተኛው ፍርድ ቤት በሽብርተኝነት ወንጀል የተፈረደባቸውን የ አንድነት ፓርቲ ም/ል ሊ/መንበር እና የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ አቶ አንዱአለም አራጌ፣ የአንድነት [...]