<?xml version="1.0" encoding="UTF-8"?>
<rss version="2.0"
	xmlns:content="http://purl.org/rss/1.0/modules/content/"
	xmlns:wfw="http://wellformedweb.org/CommentAPI/"
	xmlns:dc="http://purl.org/dc/elements/1.1/"
	xmlns:atom="http://www.w3.org/2005/Atom"
	xmlns:sy="http://purl.org/rss/1.0/modules/syndication/"
	xmlns:slash="http://purl.org/rss/1.0/modules/slash/"
	>

<channel>
	<title>Official Site for Ginbot 7 Movement for Justice, Freedom and Democracy</title>
	<atom:link href="http://www.ginbot7.org/feed/" rel="self" type="application/rss+xml" />
	<link>http://www.ginbot7.org</link>
	<description>Ethiopia</description>
	<lastBuildDate>Sat, 18 May 2013 17:59:23 +0000</lastBuildDate>
	<language>en-US</language>
	<sy:updatePeriod>hourly</sy:updatePeriod>
	<sy:updateFrequency>1</sy:updateFrequency>
	<generator>http://wordpress.org/?v=3.4.1</generator>
		<item>
		<title>ሆድ ያባውን ብቅል ያወጣዋል</title>
		<link>http://www.ginbot7.org/2013/05/16/%e1%88%86%e1%8b%b5-%e1%8b%ab%e1%89%a3%e1%8b%8d%e1%8a%95-%e1%89%a5%e1%89%85%e1%88%8d-%e1%8b%ab%e1%8b%88%e1%8c%a3%e1%8b%8b%e1%88%8d/</link>
		<comments>http://www.ginbot7.org/2013/05/16/%e1%88%86%e1%8b%b5-%e1%8b%ab%e1%89%a3%e1%8b%8d%e1%8a%95-%e1%89%a5%e1%89%85%e1%88%8d-%e1%8b%ab%e1%8b%88%e1%8c%a3%e1%8b%8b%e1%88%8d/#comments</comments>
		<pubDate>Thu, 16 May 2013 18:20:32 +0000</pubDate>
		<dc:creator>admin</dc:creator>
				<category><![CDATA[G7 Editorial]]></category>
		<category><![CDATA[Slider Post]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.ginbot7.org/?p=5107</guid>
		<description><![CDATA[ህወሃት በእሱና በራሱ ጉጅሌ አባላቶቹና ሚዲያዎቹ “በአገራችን ታሪክ ያልታየ ክስሰት በዋናነት ዜጎች በአንድነት፣ ከድህነት በማውጣት በደስታ የተሞላ ህይወትን ለማምጣት የኢኮኖሚ እድገታችን እያደገ ነው ይለናል” ይህ በሬዲዮ አዲስ አበባ፣ በሬዲዮ ኢትዮጵያ እና በሬዲዮ ፋና ብቻ ነው። ይህ ውሸት እንደተጠበቀ ሆኖ አዲሱ የለውጥ ምእራፍ ደግሞ የወያኔ ቡችሎች በየጊዜው ከህወሃት መጋረጃ በስተጀርባ ያለውን የተደበቀውን እውነት ወይም ግንቦት 7 [...]]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<p><a href="http://www.ginbot7.org/wp-content/uploads/2011/12/Weekly_Editorial_Tumbnail.jpg"><img class="alignleft  wp-image-310" title="Weekly_Editorial_Tumbnail" src="http://www.ginbot7.org/wp-content/uploads/2011/12/Weekly_Editorial_Tumbnail.jpg" alt="" width="102" height="98" /></a>ህወሃት በእሱና በራሱ ጉጅሌ አባላቶቹና ሚዲያዎቹ “በአገራችን ታሪክ ያልታየ ክስሰት በዋናነት ዜጎች በአንድነት፣ ከድህነት በማውጣት በደስታ የተሞላ ህይወትን ለማምጣት የኢኮኖሚ እድገታችን እያደገ ነው ይለናል” ይህ በሬዲዮ አዲስ አበባ፣ በሬዲዮ ኢትዮጵያ እና በሬዲዮ ፋና ብቻ ነው። ይህ ውሸት እንደተጠበቀ ሆኖ አዲሱ የለውጥ ምእራፍ ደግሞ የወያኔ ቡችሎች በየጊዜው ከህወሃት መጋረጃ በስተጀርባ ያለውን የተደበቀውን እውነት ወይም ግንቦት 7 ሲል የነበረውን የሚያረጋግጡ መረጃዎችን መስማት መጀመራችን ነው።</p>
<p>ህወሃታዊ መነቃቃትን ለማምጣት ደካሞችንና ለሆዳቸው ያደሩ ባለስልጣናቱን ሰብስቦ ስለ እድገት ጎዳናና ኃይል የሚያመረቁ ትሩፋቶችን በሚዲያዎቹ ያስነግራል። የዜጎችን የስነ ልቦና ውድቀት በከፍተኛ ደረጃ የሚፈልገው ህወሃት ባሪያዎቹንና አገልጋዮቹን በጥቅማጥቅም በማሸነፍ እውነትን ይደብቁለት ዘንድ ሁሌም ሙከራ ያደርጋል። አንዱም ተሳክቶለት አያውቅም እንጅ።</p>
<p>የኢትዮጵያ ሕዝብ ጠላት የሆነው ህወሃትና የእነሱ ተላላኪ ወያኔዎች ጦር ሰብቀው፣ መሣሪያ ወድረውና በከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲያቸው ተጠቅመው ሀገሪቷን እና ህዝቡን ከፋፍለው በዘር ካርድ ተጫውተው የስልጣን እድሜያቸውን ማራዘም ተቀዳሚ አጀንዳቸው እንጂ መቼም ስለ ኢትዮጵያ አንድነትና እድገት አስበውም አልመውትም አይውቁም፡፡ የሶማሊያው ክልል ፕሬዝዳንት አብዲ ሙሃመድ የተናገረውም ይህንኑ ነው ተደጋገመ እንጂ።</p>
<p>የከፋፍለህ ግዛ የጫካ ፖሊሲያቸውን ተጠቅመው ሀገሪቷን እንደተቆጣጠሩ ለመዝለቅ በማስብ የግል የሥልጣን እርካታቸውን ለመጠበቅ ብቸኛ ስልት ሆኖ ያገኙት የሶማሊያ ፕሬዝዳንቱ እንደሚሉት ለሶማሊያው “አማራው፣ ኦሮሞው፣ ጉራጌው፣ አፋሩ ከተባበሩ ለሶማሊያ አይመቹም። ስለዚህ ህወሃትን ደግፉና እነሱን ውጉ፤ አማራውና ኦሮሞው መቼም አይስማሙም።” በዚሁ ያልተገራ አንደበታቸው ደግሞ የህወሃቶቹ የአማራ ጎጅሌ ተላላኪ ባለስልጣናት አማራ ክልል ይሄዱና “የሶማሊያና የኦሮሞው ሰርቶ አደር ህዝብ የእንገንጠል ጥያቄ ሊያቀርቡብህ ነው” ይላሉ፤ ለባለታሪኩ የኦሮሞ ህዝብም ሄደው “አማራ ሊገዛችሁ ነው” የሚል ቆሻሻ የዘርን ክፍፍል መሰረት ያደረገ ፖለቲካዊ፣ ያልበሰለ ራእያቸውን ለማስፈጸም ሺ ምላስ ይሆናሉ።</p>
<p>የኢትዮጵያ ህዝብ በረዥም የታሪክ ዘመኑ ውስጥ በተደጋጋሚ የሚፈታተኑትን ጠላቶቹንና ተላላኪዎቹን የተንኮል አጀንዳ ቀድሞ ስለሚያውቅ ልዩነቱን አስወግዶና ቅድሚያ ለሀገሩ፣ ለአንድነቱ ሰጥቶ መሰሪ ጥቃታቸውን በማክሸፍና በማኮላሸት ረገድ ከፍተኛ ሚና ያለው ህዝብ፣ በእነዚህ የህወሃት/ኢህአዴግ የዘር ድብቅ አጀንዳ አይንበረከክም አይከፋፈልም። አማራውም፣ አሮሞውም፣ ጉራጌውም፣ ትግሬውም፣ ቤንሻንጉሉም፣ ደቡቡ አንድ ነው። ተከባብሮ ያለ እና የሚኖር ታላቅ ህዝብ በመሆኑ ከጠላቶቹ ህወሃት ከሀገር አጥፊ ዘረኞች የሚመጣበትን ቀድሞውንም ጠንቅቆ ያውቀዋልና አይገርመንም፡፡</p>
<p>ባለ ብዙ ምላሱ የወያኔ መንግስት መርዶ ነጋሪ እየሆኑ ያስቸገሩት ግለገል ፍየሎች የዚሁ የከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲ በሽታ ተጠቂ (victim) ናቸው። ብቻቸውን በተለቀቁ፣ ተንፍሱ በተባሉ ጊዜ በጀሮዎቻቸው የሚሰማቸው የተደበቀውን የእውነት ያለህ ጩኸት ነው የሚናገሩት። የህዝባቸውን በደል፣ ሰቆቃ እና የወያኔን እውነተኛ ገፅታና ያለበትን ተጨባጭ የዕድገትና የልማት ሁኔታ ያወጣሉ፣ ይናገራሉ።</p>
<p>ፕሬዚዳንቱ እፎይ ብሎ አዩኝ አላዩኝ ሳይል ያደረገው ንግግርም “ እኛ እንዳደግን ፣ ጥሩ ደረጃ ላይ እንደደረስን ተደርጎ በየጊዜው የሚቀርበው ሪፖርት ፍጹም ትክክል ያልሆነ ውሸት ነው። አሁን በእጄ የያዝኩት ሪፖርት እውነት ስለመሆኑ እርግጠኞች አይደለንም፤ ከአሁን በፊት ይቀርቡ የነበሩ ሪፖርቶችም እንዲሁ ናቸው። ግምገማ ለማለፍ ተብሎ በውሸት የተሞሉ በቁጥር የታጀቡ የውሸት ሪፖርቶች ናቸው የሚቀርቡት እንጅ እኛ በድህነት አረንቋ ውስጥ ነን ” ብሏል። የሚገርመው ፕሬዝዳንቱ ይህንን ውሸት ህዝብ የሚያውቀው አልመሰለውም፤ ለሁሉም በርታ አይዞህ ሆድ አይባስህ እኛም እያልን ያለነው ይህኑን አይን ያወጣ ውሸት እንታገለው ነው የምንለው።</p>
<p>አቶ አብዲና ሌሎችም ለሆዳችሁ ያደራችሁ ባለሰልጣናት ራሳችሁን ቀይሩ ውስጣችሁን አውሩ በታሪክ ተጠያቂ አትሁኑ፣ ህሊናችሁን አዳምጡ እንጂ ለህዝብ ጠላት ለሆነው የህዝብ ድጋፍ ከሌለው ለህወሃት ፍርፋሪ በማደር ሀገራችን ለማጥፋት ሁሌ ከሚያስቡ ከህወሃት ቡድኖች ጋር አብራችሁ ወገንን ማታለልና በዘር ካርድ መጫዎት ይብቃችሁ። የዲሞክራሲ ሃይሉን ጎራ ተቀላቀሉ፣ መረጃ አቃብሉ።</p>
<p>የወያኔ እውነተኛ ገፅታ ራሳቸውም እንደሚያረጋግጡት ይህ በመሆኑ፣ በየቦታው ዜጋን በማፈናቀል ህዝብ በሀገሩ ስደተኛ እንዲሆን ፊትም የጀመረውን ድብቅ ሥራ አማራውን በማሰደድ ያላቸውን ጥላቻ በእጥፍ በማሳደግ በርካታ አባዎራዎችን በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች ህይዎታቸው ጉስቁል እንዲሆን እያደረጉ ነው። ታዲያ ይህን እውነት እየሰማን እሰከ መቼ እንተኛ ይሆን? ግንቦት 7 ንቅናቄ ተነሱ ኑ! ተቀላቀሉን ብለናል።</p>
<p>ወያኔን ማስወገድ የሁሉም ብሄሮች ጥቅም ነው። ሁሉም ህዝብም፣ ሁሉም ፓርቲ በወያኔ መወገድ ይስማማል። ታዲያ ማን ያስወግደው? ከጥንት ጀምሮ ብዙ ትውልድ ሀገሩን ከውስጥና ከውጭ ወራሪ ለመታደግ በዚህች የኢትዮጵያ ምድር ላይ መሰዋእት ከፍሏል፡፡ ወጥቷል፣ ወርዷል አልፏል፡፡ የሰው ልጅ ተፈጥሮ የለገሰችውን የቅብብሎሽ ህግ ተቀብሎ ለነጻነቱ፣ ለማንነቱ መከበር እምቢተኝነትን ሲቀባበል፣ ሲተካካ ኖሯል፡፡ ወደፊትም ይኖራል፡፡ በዚህ የአሁኑ ሂደት ደግሞ እኛ ባለተራዎች ነን እማማ ኢትዮጵያን ከህወሃት መንጋዎች መንጋጋ ፈልቅቆ የማውጣት! ስለዚህ ለነጻነታችን ከሰማይ የሚወርድ ምንም አይነት መና የለም። እኛው ለእኛው ለራሳችን መሰዋእት ከፍለን ወያኔን እናስወገድ ዘንድ ትግሉ፣ ወቅቱ አሁን ነው።</p>
<p><strong>ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!</strong></p>
<p>&nbsp;</p>
]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ginbot7.org/2013/05/16/%e1%88%86%e1%8b%b5-%e1%8b%ab%e1%89%a3%e1%8b%8d%e1%8a%95-%e1%89%a5%e1%89%85%e1%88%8d-%e1%8b%ab%e1%8b%88%e1%8c%a3%e1%8b%8b%e1%88%8d/feed/</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>ግንቦት ሰባት የትግል ቃልኪዳን የሚታደስበት ቀን ነዉ!!</title>
		<link>http://www.ginbot7.org/2013/05/16/%e1%8c%8d%e1%8a%95%e1%89%a6%e1%89%b5-%e1%88%b0%e1%89%a3%e1%89%b5-%e1%8b%a8%e1%89%b5%e1%8c%8d%e1%88%8d-%e1%89%83%e1%88%8d%e1%8a%aa%e1%8b%b3%e1%8a%95-%e1%8b%a8%e1%88%9a%e1%89%b3%e1%8b%b0%e1%88%b5/</link>
		<comments>http://www.ginbot7.org/2013/05/16/%e1%8c%8d%e1%8a%95%e1%89%a6%e1%89%b5-%e1%88%b0%e1%89%a3%e1%89%b5-%e1%8b%a8%e1%89%b5%e1%8c%8d%e1%88%8d-%e1%89%83%e1%88%8d%e1%8a%aa%e1%8b%b3%e1%8a%95-%e1%8b%a8%e1%88%9a%e1%89%b3%e1%8b%b0%e1%88%b5/#comments</comments>
		<pubDate>Thu, 16 May 2013 08:15:22 +0000</pubDate>
		<dc:creator>admin</dc:creator>
				<category><![CDATA[Press Release]]></category>
		<category><![CDATA[Slider Post]]></category>
		<category><![CDATA[አማርኛ ዜናና መግለጫ]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.ginbot7.org/?p=5105</guid>
		<description><![CDATA[ግንቦት ሰባት የትግል ቃልኪዳን የሚታደስበት ቀን ነዉ!! ጋዜጣዊ መግለጫ  የኢትዮጵያ ህዝብ በታሪክና በባህል ትስስሩ፤ በረጂም ግዜ አብሮ መኖር ልምዱና እንዲሁም በነፃነትና ዲሞክራሲ ትግል ምዕራፉ ዉስጥ በጋራ ያፈራቸዉና በባለቤትነት የሚጋራቸዉ የተለያዩ እሴቶች አሉት። ቆየት ያሉትንና በኩራት የሚያስፈነድቀንን የአድዋን ድል ወይም በኃዘን ስሜታችንን ሁሌም የሚቆጠቁጡዉን የሰማዕታት ቀን ትተን የአጭር ግዜ ትዉስታችንን ስንፈትሽ ፊታችን ላይ እንደ መስታወት ድቅን [...]]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<h1 style="text-align: justify;">ግንቦት ሰባት የትግል ቃልኪዳን የሚታደስበት ቀን ነዉ!!</h1>
<p style="text-align: justify;">
ጋዜጣዊ መግለጫ</p>
<p style="text-align: justify;">
<p style="text-align: justify;"> የኢትዮጵያ ህዝብ በታሪክና በባህል ትስስሩ፤ በረጂም ግዜ አብሮ መኖር ልምዱና እንዲሁም በነፃነትና ዲሞክራሲ ትግል ምዕራፉ ዉስጥ በጋራ ያፈራቸዉና በባለቤትነት የሚጋራቸዉ የተለያዩ እሴቶች አሉት። ቆየት ያሉትንና በኩራት የሚያስፈነድቀንን የአድዋን ድል ወይም በኃዘን ስሜታችንን ሁሌም የሚቆጠቁጡዉን የሰማዕታት ቀን ትተን የአጭር ግዜ ትዉስታችንን ስንፈትሽ ፊታችን ላይ እንደ መስታወት ድቅን እያሉ እራሳችንን ከሚያሳያዩን ቀኖች ዉስጥ አንዱና ዋነኛዉ ግንቦት 7 1997 ዓም የዋለዉ ታሪካዊ ቀን ነዉ። ይህ ቀን በኢትዮጵያ ህዝብ የፍትህ፤ የነጻነትና የዲሞክራሲ ትግል ሂደት ዉስጥ የፀሐይንና የጨረቃን ያክል ገዝፎና ደምቆ የሚታይ ልዩ ቀን ነዉ። ግንቦት ሰባት 1997 ዓም የኢትዮጵያ ህዝብ ብሩህና የወደፊቱን አመላካች የሆነ ፍሬያማ ጉዞ ጀምሮ ፍሬዉን ከማየቱ በፊት የጀመረዉን ጉዞ እንዲያቋርጥ የተገደደበትና ለዘመናት አንገቱ ላይ አንደ ቀንበር ተጭኖበት የቆየዉን የአምባገነኖች ክፉ ጫና አዉልቆ ለመጣል ሲዘገጅ ዝግጅቱ በአጭር የተቀጨበት ጨለማና ተስፋ፤ ቁጭትና ጽናት አንድ ላይ የታዩበት ትንግርታዊ ቀን ነዉ።</p>
<p style="text-align: justify;">ግንቦት 7 ቀን 1997 ዓ.ም. በዛሬዉና ለወደፊት በተከታታይ በሚመጣዉ ኢትዮጰያዊ ትዉልድ ልብ ውስጥ ተስፋን፤ ልበሙሉነትን፤ ጅግንነትንና መስዋዕትነትን እየጠቆመ ለዘለአለም የሚዘከር ቀን ነዉ። ግንቦት ሰባት የኢትዮጵያ ህዝብ በጠመንጃ ኃይል እላዩ ላይ የተጫነበትን ዘረኛ አምባገነን ስርዐት በምርጫ ካርድ ጥሎ ለእድገት፤ ለሰላምና ለአንድነቴ ይበጁኛል ያላቸዉን መሪዎቹን መርጦ ስልጣን ወንበር ላይ ለማስቀመጥ ታሪካዊ እርምጃ የወሰደበትና አርቆ አሰተዋይነቱን ለአለም ህዝብ ያሳየበት ቀን ነዉ። በሌላ በኩል ደግሞ ግንቦት ሰባት አምባገነኑ የወያኔ አገዛዝ ለህዝብ ምርጫና ፍላጎት የማይገዛና የስልጣን ዘመኔን ያሳጥርብኛል ብሎ ያሰበዉን ሁሉ ያለ ርህራሄ የሚገድል ጸረ ህዝብ ኃይል መሆኑን ያረጋገጠበት ቀን ነዉ።</p>
<p style="text-align: justify;">ግንቦት ሰባት ቀን የኢትዮጵያ ህዝብ ቋንቋ፤ ክልልና ኃይማኖት ሳይከፋፍሉት ከዳር ዳር አንደ አንድ ሰዉ በመቆም ያሳየዉ የኢትዮጵያዊነት፤የአንድነትና፣ የወንድማማችነት ስሜት በጻነትና በዲሞክራሲ ትግላችን ታሪክ ዉስጥ ለዘለአለም ሲታወሱ የሚኖሩ የህዝብ ትዉስታዎች ናቸዉ። ሆኖም ግንቦት ሰባት የኢትዮጵያ ህዝብ አንድነቱንና ለዲሞክራሲ ዝግጁ መሆኑን ያረጋገጠዉን ያክል ጠላቶቹም እነሱ ስልጣን ላይ እስካሉ ድረስ ኢትዮጵያ ዉስጥ ሊኖር የሚችለዉ ዲሞክራሲ ከእነሱ ዉጭ ሌላ ማንንም ወደ ስልጣን የማያመጣ መሆኑን በጠመንጃ ኃይል ያረጋገጡበት ቀን ነዉ።</p>
<p style="text-align: justify;">ግንቦት ሰባት 1997 ዓም የወያኔ አገዛዝ በኢትዮጵያ ህዝብ ልብና አዕምሮ ዉስጥ መንግስትን በምርጫ ካርድ መቀየር እንችላለን የሚል ስሜት እንዳይለመልም በህግ ሽፋን ተከታታይ እርምጃዎችን መዉሰድ የጀመረበት ቀን ሲሆን፤ የኢትዮጵያ ህዝብም በበኩሉ ነጻ የመገናኛ ተቋሞች፤ ነጻ ፍርድ ቤት፤ገለልተኛ የምርጫ ተቋምና ለህገ መንግስት የሚገዛ ጦር ኃይል በሌለበት ሁኔታ ዉስጥ የሚካሄዱ ምርጫዎች እንደማይጠቅሙት አዉቆ ወያኔን ማስገደድ የሚችል የትግል እስትራቴጂ የቀየሰበት ቀን ነዉ።</p>
<p style="text-align: justify;">ግንቦት 7 ቀን 2000 ዓም የኢትዮጵያ ህዝብ ወያኔ በጠመንጃ ኃይል የነጠቀውን መብት በተቀነባበረ ሁለገብ ህዝባዊ ትግል ለማስመለስና ኢትዮጵያ ዉስጥ የፖለቲካ ስልጣን ምንጭ ህዝብ ብቻ መሆኑን ለማረጋገጥ አዲስ የትግል ስልትና ግንቦት ሰባት የፍትህ፤የነጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄን አምጦ የወለደበት ቀን ነዉ። የግንቦት 7 ብቸኛ አላማ ኢትዮጵያ ዉስጥ መንበረ ስልጣን ትክክለኛ ባለቤቱ ወደ ሆነዉ የኢትዮጵያ ህዝብ እጅ ዉስጥ እንዲገባ ማድረግና የወያኔን አገዛዝ አገራችን ዉስጥ የመጨረሻዉ አምባገነን ስርአት ማድረግ ነዉ። ግንቦት 7 ይህ አላማዉ ግቡን እስኪመታ ድረስ ህዝባዊ ትግሉን እንደሚገፋበት ለኢትዮጵያ ህዝብ የገባዉ ቃል ኪዳን ዛሬም ህያዉ መሆኑን ያረጋግጣል።</p>
<p style="text-align: justify;">ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!</p>
]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ginbot7.org/2013/05/16/%e1%8c%8d%e1%8a%95%e1%89%a6%e1%89%b5-%e1%88%b0%e1%89%a3%e1%89%b5-%e1%8b%a8%e1%89%b5%e1%8c%8d%e1%88%8d-%e1%89%83%e1%88%8d%e1%8a%aa%e1%8b%b3%e1%8a%95-%e1%8b%a8%e1%88%9a%e1%89%b3%e1%8b%b0%e1%88%b5/feed/</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>ማን ነው ወንጀለኛው?</title>
		<link>http://www.ginbot7.org/2013/05/10/%e1%88%9b%e1%8a%95-%e1%8a%90%e1%8b%8d-%e1%8b%88%e1%8a%95%e1%8c%80%e1%88%88%e1%8a%9b%e1%8b%8d/</link>
		<comments>http://www.ginbot7.org/2013/05/10/%e1%88%9b%e1%8a%95-%e1%8a%90%e1%8b%8d-%e1%8b%88%e1%8a%95%e1%8c%80%e1%88%88%e1%8a%9b%e1%8b%8d/#comments</comments>
		<pubDate>Fri, 10 May 2013 22:17:16 +0000</pubDate>
		<dc:creator>admin</dc:creator>
				<category><![CDATA[G7 Editorial]]></category>
		<category><![CDATA[Slider Post]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.ginbot7.org/?p=5097</guid>
		<description><![CDATA[በከፍተኛ ደረጃ የህዝብ እምነት ያጣው የካንጋሮው ፍርድቤት ምንም አይነት የህግ ወይም የሞራል የበላይነት ሳይኖረው፤ የህሊና እስረኞቹን የእድሜ ልክና እና ሌሎች ቅጣቶችን እንዴት ሊሰጥ ይችላል? ማነው ፈራጁ? ማንስ ነው ተፈራጁ? ማን ነው ጥፋተኛው። ህግን ያዋረደ? ወይስ ስለነጻነት፣ ስለ ዲሞክራሲ አቤት ያለ? በፍትህ እና በፍትህ ፈላጊዎች ላይ እየቀለደ እና ተቋሙን እያዋረደ የሚገኘው ወያኔ ዛሬም እንደትላንቱ ሌላ የበደል [...]]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<p><a href="http://www.ginbot7.org/wp-content/uploads/2011/12/Weekly_Editorial_Tumbnail.jpg"><img class="alignleft  wp-image-310" title="Weekly_Editorial_Tumbnail" src="http://www.ginbot7.org/wp-content/uploads/2011/12/Weekly_Editorial_Tumbnail.jpg" alt="" width="102" height="98" /></a>በከፍተኛ ደረጃ የህዝብ እምነት ያጣው የካንጋሮው ፍርድቤት ምንም አይነት የህግ ወይም የሞራል የበላይነት ሳይኖረው፤ የህሊና እስረኞቹን የእድሜ ልክና እና ሌሎች ቅጣቶችን እንዴት ሊሰጥ ይችላል? ማነው ፈራጁ? ማንስ ነው ተፈራጁ? ማን ነው ጥፋተኛው። ህግን ያዋረደ? ወይስ ስለነጻነት፣ ስለ ዲሞክራሲ አቤት ያለ?</p>
<p>በፍትህ እና በፍትህ ፈላጊዎች ላይ እየቀለደ እና ተቋሙን እያዋረደ የሚገኘው ወያኔ ዛሬም እንደትላንቱ ሌላ የበደል ጩኸት ከተባዳዮቹ ለበዳዮቹ እንዳይሰማ በጉጅሌ “ዳኞ” ተብየዎች አማካኝነት ውሳኔ ሰጥቷል። እውነተኛ ፍትህ ሀገራችን ውስጥ ጠፍቶ መቀበሩን ለማሳየት ሲል ባስቀመጣቸው የፍትህ ተወናያን ዳኞች አማካኝነት አረፍን እንቀመጥ ዘንድ ፍትህን ትመኙታላችሁ እንጅ አታገኙትም ሲል መልክቱን በአሻንጉሊቶች ፍርድቤቶች አማካኝነት አስተላልፏል።</p>
<p>የገዥው ፓርቲ ጉዳይ አስፈፃሚ ዳኞች ሰሞኑን የሰጡት ፓለቲካዊ ውሳኔ የአገልጋይነታቸውን ታማኝነት ማረጋገጫ እንጅ፤ ኢትዮጵያ ውስጥ ህወሃት እያለ ፍትህና ፍትህ ፈላጊዎችን ማገናኘት የማይታሰብ መሆኑን በድጋሜ ተረጋግጧል፡፡ ፍትህ የነፃነትና የእኩልነት ማረጋገጫ፤ ግለሰቦችና ቡድኖች በሥርዓት እንዲኖሩ ማድረጊያ እና የአንድ ማኅበረሰብ የሞራል እሴቶች ተፈፃሚነት ማሳያ ነበር፡፡ ፍትህ በሌለበት ነፃነት፣ እኩልነት፣ ሰላም፣ ልማት እና ዲሞክራሲ ትርጉም የላቸውም፡፡</p>
<p>ለዚህም ነው ራሱ የፍትህ ስርአቱ ተቋም የካድሬዎች እስረኛ ነው የምንለው። ተቋማት ነጻ አልወጡም፣ ህዝባችን በጎጠኝነት የአገዛዝ አባዜ ይሰቀያል። በማንነቱ ይሰደዳል፣ ይታሰራል። ታዲያ ማን ነው ጥፋተኛው? በዳዩ ወይስ ተበዳዩ?</p>
<p>ዜጎች በሀገራቸው የመኖር፣ የመናገር ፍትህ የማግኘት ተስፋቸው እንደገና ተቀብሯል። ተዋርደናል፤ ውርደት እስከ መቼ? ኢትዮጵያዊ እምቢተኝነታችን፣ ክብርና ኩራታችን፣ ታሪካችን በወያኔዎች ተደፍሯል። በፋሲካ የጀግናው ሰማእታት የአቡነ ጴጥሮስ የመታሰቢያ ሀውልት ለረጅም ጊዜ ከተቀመጠበት፣ ከመታሰቢያነቱ ስፍራ አሻራነቱ ተነስቷል። በዚሁ ዋዜማ እነ አንዷለምአራጌ፣ እስክንድር ነጋ፣ ክንፈሚካኤል ደበበ፣ ናትናኤል መኮነን፣ ምትኩ ዳምጤ፣ ዮሃንስ ተረፈ እና ሻምበል የሺዋስ ይሁን አለም ላይ በፋሲካ ዋዜማ አይሁዶች የህሊና እስረኞቹ ይሰቀሉላቸው ዘንድ ፈረዱ።</p>
<p>በፋሲካ በወያኔ ጨለማ ቤት ውስጥ የተዘጉ፣ የተረሱ ዜጎችም አሉ እነ በቀለ፣ ርእዮት፣ ውብሸት እና እነ ጀኒራል ተፈራ ማሞ እና ሌሎቹም። አሁንም በፋሲካ ህዝቡ እየተሰደደ፣ እየተፈናቀለ ነው። በአንጻሩ አይሁዶች እጃቸውን በደም እየታጠቡ ከደሙ ንጹህ ለመሆን ሲሉ ውስኪ ሲራጩ ይታያሉ። ማን ነው ወንጀለኛው?</p>
<p>ኢህአዴግ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን በሾማቸው “ዳኞች” ተብየዎች ስም እያፈራረሳት ነው። ትውልድን የቁም እስረኛና አንገቱን እንዲደፋ እንዲሸማቀቅ እያደረጉት ነው። ሀገራችን በወረበሎች አንገቷን ደፍታ የወያኔዎች መሳለቂያ ሆናለች። እናድናት።</p>
<p>የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ፡ የበደል ትልቅና ትንሽ የለውም። በወያኔ ያልተገረፈ፣ ያልተሰደደ፣ ያልተገደለ፣ ያልታሰረ፣ ያልቆሰለ፣ ሀብት ንብረቱን ያልተወረሰ፣ ያልተዋረደ፣ አንገቱን ያልደፋ፣ ያልተበደለ፣ ፍትህን ያልተነፈገ፣ የእምነት ነጻነቱን ያልተገፈፈ ዜጋ የለም። ያጣነው ብዙ ነው። ያጣነውን የማስመለስ ኢትዮጵያዊ ግዴታ አለብን። ሀገራችን ኢትዮጵያ ይህን ውርደትና መከራ እና አይን ያወጣ ጭካኔ ዘረኝነት ብዝቶና ተባብሶ ህልውናዋ ከመጥፋቱ ዜጎቿ የህሊና እስረኞች ሁነው ፍትህ አጥተው ከማለቃቸው በፊት የሚደርሱላት ጀግኖችን ትሻለች።</p>
<p>ወጣቱ ትውልድ ከገባበት የፍርሃት አረንቋ ወጥቶ፣ ፍርሃቱን በጀግነነቱ በጥሶ ኢትዮጵያንና ወገኑን ለማዳንና ነጻነትን በመሰዋእቱ ከፍሎ ለሀገራችን ብርሃን የመሆኛ ጊዜው አሁን ነው። እምቢ ብለህ የነጻነት ተስፋ የሆኑ ህዝባዊ ሃይሎችን ተቀላቀል። ትግል በአንድ ጀምበር የሚያልቅ አይደለም። በርካታ ረጅምና አስቸጋሪ ፈተናዎች ያሉበት፣ የሚጠበቁበት ነው። ቁም ነገሩ ይህንን የተጋረደብህን ፈተና ተፈትነህ ማለፉ ላይ ነው ጀግንነቱ። እንዲህ አይነት ፈተና አምባገነን መንግስት እሰከ አለ ድረስ ለነጻነት፣ ለዲሞክራሲና ለፍትህ መከበር በሚነሱ ሃይላት ላይ የሚኖርና የሚቀጥል በመሆኑ፤ በወያኔ በሚደርስብን የስቃይ ውርጅብኝ ሳንበረከክ ለፍትህ ስርአት መከበር ለህግ የበላይነት መስፈን ለሀገር አንድነት የምናደርገውን ትግል በማጠናከር መቀጠልና ግንባር ቀደም ታጋዮች መሆን ይኖርብናል።</p>
<p>ግንቦት 7 የፍትህ የዲሞክራሲና የነጻነት ንቅናቄ ለፍትህ መቆም ሲል ነፃነቱንና ሀገሩን የሚወድ ዜጋ ሁሉ በማናቸውም መንገድ ወያኔን የመታገል ሞራላዊ ግዴታ አለበት ይላል፡፡ ከትግሉ ባሻገር በነጻነት ታጋዮች ላይ የሀሰት ምስክር የሚሰጡትን፣ ፍትህን የሚየዛቡ ዳኞችና አቃቤዓነ-ህግን የክህደት ሥራዎቻቸውን መዝግቦ መያዝ፣ በዓይነ ቁራኛ መከታተል የሁላችንም ግዴታ ነው፡፡</p>
<p>ህዝብ በሃሰት ምስክሮች፣ ዳኞችና አቃቢያነ-ህግ ላይ ቁጣውን የሚገልጽበት ጊዜ ተቃርቧል፡፡ በወያኔ ወኔ ቢስ አድርባዮች ፍትህ ስትቀበር፣ ዘረኝነት ሲወደስ፣ ታጋዮቻችን ሲገደሉ፣ ሲንገላቱና ሲበደሉ ሲታሰሩ ማየት በቃን ብለናል፡፡ ፍትህን የሚያረክሱትን የወያኔ ቅጠረኞችን በቁርጠኛነት፣ አምርረን እንታገላለን፡፡ የወያኔ ቡችላ ፍርድቤት አገልጋዮች ወዮላችሁ! ያላገጣችሁበት ፍትህ እናንተን ባልጠበቃችሁት ሁኔታ፣ ግዜና ቦታ ትጠየቃችኋለች፡፡ ስለዚህ ራሳችሁን ከቁም እስረኝነትና አገልጋይነት፣ አሽከርነትና ከአደርባይነት ታወጡ ዘንድ ጊዜው አልረፈደባችሁም። እድሉን የመጠቀም ሃላፊነት የእናንተ ነው። እኛ ግን በቃ ብለናል።</p>
<p>ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!</p>
<p>&nbsp;</p>
<p>&nbsp;</p>
]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ginbot7.org/2013/05/10/%e1%88%9b%e1%8a%95-%e1%8a%90%e1%8b%8d-%e1%8b%88%e1%8a%95%e1%8c%80%e1%88%88%e1%8a%9b%e1%8b%8d/feed/</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>Dr Berhanu Nega&#8217;s intervew with France based Radio about the imprisonment of Eskinder Nega and the judicial system in Ethiopian, May 2013</title>
		<link>http://www.ginbot7.org/2013/05/08/dr-berhanu-negas-intervew-intervew-with-france-based-radio-about-the-imprisonment-eskinder-nega-and-the-judicial-system-in-ethiopian-may-2013/</link>
		<comments>http://www.ginbot7.org/2013/05/08/dr-berhanu-negas-intervew-intervew-with-france-based-radio-about-the-imprisonment-eskinder-nega-and-the-judicial-system-in-ethiopian-may-2013/#comments</comments>
		<pubDate>Wed, 08 May 2013 13:58:10 +0000</pubDate>
		<dc:creator>admin</dc:creator>
				<category><![CDATA[Slider Post]]></category>
		<category><![CDATA[Video]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.ginbot7.org/?p=5088</guid>
		<description><![CDATA[]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<p><iframe width="640" height="360" src="http://www.youtube.com/embed/aj_xv6vYGpU?feature=player_detailpage" frameborder="0" allowfullscreen></iframe></p>
]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ginbot7.org/2013/05/08/dr-berhanu-negas-intervew-intervew-with-france-based-radio-about-the-imprisonment-eskinder-nega-and-the-judicial-system-in-ethiopian-may-2013/feed/</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>የወያኔ ልማት ሰዋዊ ሽታ የለውም</title>
		<link>http://www.ginbot7.org/2013/05/02/%e1%8b%a8%e1%8b%88%e1%8b%ab%e1%8a%94-%e1%88%8d%e1%88%9b%e1%89%b5-%e1%88%b0%e1%8b%8b%e1%8b%8a-%e1%88%bd%e1%89%b3-%e1%8b%a8%e1%88%88%e1%8b%8d%e1%88%9d/</link>
		<comments>http://www.ginbot7.org/2013/05/02/%e1%8b%a8%e1%8b%88%e1%8b%ab%e1%8a%94-%e1%88%8d%e1%88%9b%e1%89%b5-%e1%88%b0%e1%8b%8b%e1%8b%8a-%e1%88%bd%e1%89%b3-%e1%8b%a8%e1%88%88%e1%8b%8d%e1%88%9d/#comments</comments>
		<pubDate>Thu, 02 May 2013 22:17:07 +0000</pubDate>
		<dc:creator>admin</dc:creator>
				<category><![CDATA[G7 Editorial]]></category>
		<category><![CDATA[Slider Post]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.ginbot7.org/?p=5078</guid>
		<description><![CDATA[የወያኔ ልማት ሰዋዊ ሽታ የለውም ሀገራችንን አንቆ የሚገዛው ወያኔ ራሱን የልማት መንግስት ነኝ በሚል ራሱን በሚጠፋ ስእል ላይ አስቀምጦል። በየአመቱ የተጋነነ እና የሌለ ነጠላ የስታቲስቲክ ዜማ እየለቀቀ ያቀርባል። በዴሞክራሲያዊ መንገድ ህጋዊ መሰረት ማግኘት ስለተሳነው በልማታዊ መዝገብ ስም ለመገኘት አይን የአወጣ ሙከራ ያደርጋል። የወያኔ ልማት ሰዋዊ ሽታ የለውም። ለዘረኛው መንግስት ልማት ማለት ብልጭልጫዊ ነገር ማሳየት እንጂ [...]]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<p>የወያኔ ልማት ሰዋዊ ሽታ የለውም</p>
<p>ሀገራችንን አንቆ የሚገዛው ወያኔ ራሱን የልማት መንግስት ነኝ በሚል ራሱን በሚጠፋ ስእል ላይ አስቀምጦል። በየአመቱ የተጋነነ እና የሌለ ነጠላ የስታቲስቲክ ዜማ እየለቀቀ ያቀርባል። በዴሞክራሲያዊ መንገድ ህጋዊ መሰረት ማግኘት ስለተሳነው በልማታዊ መዝገብ ስም ለመገኘት አይን የአወጣ ሙከራ ያደርጋል።</p>
<p>የወያኔ ልማት ሰዋዊ ሽታ የለውም። ለዘረኛው መንግስት ልማት ማለት ብልጭልጫዊ ነገር ማሳየት እንጂ የሰውን፣ የህዝቡን ጉስቁል ኑሮ መቀየር ማሻሻል መሆኑን አያውቅም። አንድ ሺ አፈናቅሎ አንድ የስርአቱን አገልጋይ ቱጃር ያከብርና አገር ለማ ይለናል። የጋምቤላን አኙዋኮች ከአያት ቅድመ አያት መሬት አፈናቅሎ በርሃብ እየቆላ፣ የአረብና ህንድ የሩዝ ሁዳድ ስላደረገው ብቻ አገር ለማ ከበሮ ደልቁ ይለናል።</p>
<p>ወያኔ ልማት ለሰው መሆኑን ወይ አያውቀውም አሊያም ረስቶታል። በአዲስ አበባና በብዙ አካባቢዎች መንደርን እያፈረሰ የሚበትናቸው ዜጎች፤ ከእነሱ ጋር እድራቸው፣ ሰንበቴያቸው፣ ማህበራቸው፣ ማህበራዊ ህይወታቸው አብሮ እንደሚፈርስ ቢያውቅም ግድ የለውም። የወያኔ ልማት ሰውን ወደተራ እንስሳነት የሚያወርድ የወሮበላ ስራ ነው።</p>
<p>ህወሃት እንደ መንግስት ሱፍ ለብሶ፣ በሌላ በኩል እንደ ኢፈርት ባለቤትነቱ ወዛደር መስሎ ውል ይፈራረማል። ኢፈርት የሚገጣጥመውን መኪና ለመከላከያ ሚኒስተር ይሸጣል፤ እንደ መንግስት በህዝብ ስም እርዳታ ይቀበላል፣ እንደ ወሮበላ ዘራፊ ስማቸውን ቀይረው ወዲያውኑ ዘረፋውን ይጀምራል። ይህን የመሰለ የዘቀጠ ውንብድና በህዝብ ንብረት ላይ እየሰሩ ሌሎችን የወያኔ ግልገሎች ደግሞ ሌቦች፣ ኪራይ ሰብሳቢዎች እያሉ ሲሳደቡ አይናቸውን አያሹም።</p>
<p>የወያኔ አለቆች ድሃ ገበሬዎችን ከመኖሪያቸው ሲያፈናቅሉ ደን ስለጨፈጨፉ ነው የሚል የፈጠራ ክስ ይፈጥሩና የኤፈርት ኩባንያዎች ኢሉ አባቦር ውስጥ የያዩን ደን እየጨፈጨፉና እያጋዩ የሚሰሩትን የዝርፊያ ማእድን ቁፈራ ልማት ነው ይሉናል።</p>
<p>ወያኔ በሚገዛት ኢትዮጵያ ባለሀብት መሆንና ሀገር አልምቶ ራስን መጥቀም ገደብና መስመር አለው። ብዙ ኢንቨስተሮች የወያኔ ባለስልጣንን በአጋርነት፣ በሸሪክነት እንዲያስገቡ ይገደዳሉ። አሊያም ሀብቱን ላለመነጠቅ የፈለገ ሀብታም ልሁን ባይ የዳጎሰ ገንዘብ ለባለስልጣናቱ እጅ መንሻ ለኪስ ተጠይቀው ይሰጣሉ። በአንጻሩ የወያኔን የሀብታምነትን ቀይ መስመር ዘለው እምቢ ያሉ እስር ቤት የተጣሉ፣ የተሰደዱ በተለይ ወያኔ ከሚጠላው የጎሳ ወገን የሆኑ ኢትዮጵያውያን ቁጥር በየቀኑ እየጨመረ፣ የልማት ተስፈኞቹ በቃሊቲና በዝዋይ እስር ቤቶች ተጨናንቀዋል።</p>
<p>ዛሬ ዛሬ ጤፍ ጠፋ ተወደደ፣ ስኳር ጠፋ ምን እንሁን፣ መብራትና ውሃ ጠፋ ፈረቃው በዛብን ሲባሉ፤ መልሳቸው አስገራሚ እና አሳዛኝ ነው፡፡ ይህ ሁሉ የጠፋው፣ የምትራቡት አገሪቱ እያደገች ስለሆነ ነው የሚል የማላገጥ መልስ ይሰጣሉ። የሚሉት እድገት ቁልቁል እንደካሮት እየጨመረ ያለውን ድህነት መሆኑን ማለታቸው ነው።</p>
<p>በኢትዮጵያ የነገሰው ደህነት፣ ከድህነቱ ጋር የተያያዘው መጠነ ሰፊ ተስፋ መቁረጥና ስደት ለወያኔ ምኑም አይደለም። ምናልባትም የአገሪቱን እድገት ያመጣው ነገር ነው በሚል መላምት የሆነ፣ የይሆናል ግምታቸውን ይሰጡናል።</p>
<p>የአደገችና የበለጸገችን ኢትዮጵያ ከመፍጠር ይልቅ በልማት ስም የግል ምቾታቸውንና ድሎቶቻቸውን ለማስጠበቅ፣ ብሎም የስልጣን ጊዚያቸውን ለማራዘም ሲሉ፤ ህዝብን ከቀዪው በማፈናቀል ለርሃብና ለስቃይ ለስደት እየዳረጉት ይገኛሉ።</p>
<p>ህወሃቶች የሀብት ክፍፍል በገጠሪቱ ኢትዮጵያ በሚል የአካባቢውን ነዋሪ በማንነቱ ምክንያት አፈናቅለው የህወሃት አባላትንና ደጋፊዎችን የመጥቀም ስትራቴጂዎችን ቀርጸው ሰፊውን የህዝብ ጉልበት እንደ መዥገር መጠው፣ በቀዪው ያፈራውን ንብረትና ገንዘብ እንኳ ሳይሰበስብ ያፈናቅሉታል። ታዲያ የትኛው የልማት ስትራቴጂ ይሆን ህዝብን ማእከል ያደረገው?</p>
<p>የተማሩ ዜጎች በተማሩበት ሙያ ሰርተው በልማቱ ሂደት ራሳቸውንና ሀገራቸውን እንዳይጠቅሙ አድረገው ራእያቸው በማጨለም በጨፍን የስርአቱ ባሪያ አገልጋይ አሊያም አጨብጫቢ እንዲሆኑ ሆነው ይቀረጻሉ፤ አሊያ ግን መጽዋት ጠባቂ ወይም ከሀገር እንዲሰደዱ ይደረጋሉ።</p>
<p>የወያኔ ልማት ህዝብ ህዝብም፣ ሰው ሰውም አይሸትም! ስለዚህም በአገር አልሚነት ስም ማንንም ማታለል አይችልም። ይህ የዝርፊያና የፈንጋይ የወያኔ ኢኮኖሚ ከራሳቸውና ከጉጅሌዎች ባለፈ ውጭ የሚጠቅመው ኢትዮጵያዊ አይኖርም።</p>
<p>ኢትዮጵያ ለሁሉም ልጆቿ የሚሆን የተፈጥሮ ጸጋ አላት። ምቹ የአየር ንብረት፣ ለም አፍርና በተስተካከለ መልከዓ ምድር የተቸረች ሀገር ነች። ልጆቿ ሁሉ የዚህ ጸጋ ባለቤት እንዳይሆኑ እና ዜጎቿ በእኩልነት ተጠቃሚ ሳይሆኑ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች ሆነው እንዲሰደዱ እያደረገ ያለው ወያኔ ነው። ወያኔ አልሚ ሳይሆን የልማት ፀርና የአንድነት ቀበኛ ነው።</p>
<p>በኢትዮጵያ ልማትም፣ እድገትም፣ እኩልነትም፣ ሰብአዊ ክብርም፣ ተስፋም፣ በሀገር መኩራትም እንዲኖር ወያኔ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ መወገድ አለበት። ግንቦት 7 የፍትህ፣ የነጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ለነዚህና ለእውነተኛ የሰበአዊ መብት መከበር፣ ሁሉም ዜጎች በሀገራቸው የትኛውም ቦታ በእኩልነት ሰርቶ የማደግ መሰረታዊ መብቶች፤ ህዝብን ማእከል ላደረገ እውነተኛ ልማት እና ሀገራችንን ከመፈራረስ አደጋ ለመታደግ ረጅሙን የትግል ጉዞ በአንድ ርምጃ ጀምሮአል፡፡ እርሰዎስ? ኑ! ተቀላቀሉን፡፡ ድህነት፣ ውርደት፣ ስደት እስከመቼ?</p>
<p>ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!</p>
<p>&nbsp;</p>
]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ginbot7.org/2013/05/02/%e1%8b%a8%e1%8b%88%e1%8b%ab%e1%8a%94-%e1%88%8d%e1%88%9b%e1%89%b5-%e1%88%b0%e1%8b%8b%e1%8b%8a-%e1%88%bd%e1%89%b3-%e1%8b%a8%e1%88%88%e1%8b%8d%e1%88%9d/feed/</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>የዘመኑ ትውልድ ሥነ-ምግባር ወዴት?</title>
		<link>http://www.ginbot7.org/2013/05/02/%e1%8b%a8%e1%8b%98%e1%88%98%e1%8a%91-%e1%89%b5%e1%8b%8d%e1%88%8d%e1%8b%b5-%e1%88%a5%e1%8a%90-%e1%88%9d%e1%8c%8d%e1%89%a3%e1%88%ad-%e1%8b%88%e1%8b%b4%e1%89%b5/</link>
		<comments>http://www.ginbot7.org/2013/05/02/%e1%8b%a8%e1%8b%98%e1%88%98%e1%8a%91-%e1%89%b5%e1%8b%8d%e1%88%8d%e1%8b%b5-%e1%88%a5%e1%8a%90-%e1%88%9d%e1%8c%8d%e1%89%a3%e1%88%ad-%e1%8b%88%e1%8b%b4%e1%89%b5/#comments</comments>
		<pubDate>Thu, 02 May 2013 22:13:32 +0000</pubDate>
		<dc:creator>admin</dc:creator>
				<category><![CDATA[Slider Post]]></category>
		<category><![CDATA[አማርኛ ዜናና መግለጫ]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.ginbot7.org/?p=5074</guid>
		<description><![CDATA[በዘመነ ካሴ አንድ ትውልድ ትውልዳዊ ፍሰቱን ጠብቆ ዘመናትን በስኬት መጓዝ ይችል ዘንድ ከቁሳዊ ሥልጣኔ ባሻገር በመንፈስ የሰለጠነ፤ በሥነግባር የታነፀና ባለራዕይ ሊሆን ይገባል። ከዚህ አኳያ በወያኔ ዘመን በሥነምግባር የታነፀ፤ ባለተስፋና በትክክል ማለም የሚችል ስነ አዕምሮና ጠንካራ ስነልቦና ያለው ትውልድ ከመፍጠር አኳያ ምን ላይ ነው ያለነው? የትውልዱ ሥነ-ምግባር በምን ልክ እየተቀረፀ ነው? ትውልዱ በጥሩ ሥነ-ምግባር ይታነጽ ዘንድ [...]]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<p><strong>በዘመነ ካሴ</strong></p>
<p>አንድ ትውልድ ትውልዳዊ ፍሰቱን ጠብቆ ዘመናትን በስኬት መጓዝ ይችል ዘንድ ከቁሳዊ ሥልጣኔ ባሻገር በመንፈስ የሰለጠነ፤ በሥነግባር የታነፀና ባለራዕይ ሊሆን ይገባል። ከዚህ አኳያ በወያኔ ዘመን በሥነምግባር የታነፀ፤ ባለተስፋና በትክክል ማለም የሚችል ስነ አዕምሮና ጠንካራ ስነልቦና ያለው ትውልድ ከመፍጠር አኳያ ምን ላይ ነው ያለነው? የትውልዱ ሥነ-ምግባር በምን ልክ እየተቀረፀ ነው? ትውልዱ በጥሩ ሥነ-ምግባር ይታነጽ ዘንድ ከፍተኛው ድርሻ የሚጠበቅባቸው ተቋማት ድርሻቸውን እየተወጡ ነውን? ካልሆነ ምን ዓይነት ነገ ይጠብቀናል? መፍትሔውስ ምንድነው?</p>
<p>በእኔ እምነት የአንድ ትውልድ ሥነምግባር በቅጡ ይታነጽ ዘንድ የሚከተሉት ተቋማት ኃላፊነት አለባቸው። ይህን ኃላፊነታቸውን ከመወጣት አኳያ ምን ሳንካ እየገጠማቸው ነው የሚለውን አያይዤ ለመጥቀስ እሞክራለሁ።</p>
<p><strong>1. ቤተሰብ</strong></p>
<p>ቤተሰብ የአንድን ማኅብረሰብ እጣ ፈንታ ለመወሰን የሚችል የሚታይና የሚዳሰስ ተቋም ነው።ጥሩ ቤተሰብ የጥሩ ማኅበረሰብ መሠረትነው። ጥሩ ማኅበረሰብ የጥሩ ሃገር መሠረትነው። ስለዚህ በአንድ ቤተሰብ ውስጥ የሚኖር ግብረገባዊ መስተጋብር፡ እናት ወይም አባት (የቤሰብ ሃላፊዎች) ልጆቻቸውን በሥነ ምግባር ለመቅረጽ የሚኖራቸው ኃላፊነት እና አደራ እጅግ ከባድ ነው። ልጆች ትምህራቸውን በደንብ እንዲከታተሉ፤ ሰው ማክበርና ሰው መውደድን፣ ሰብዓዊነትን፣ ቅንነትን፣ “ይቻላል” ባይነትን፣ ምክንያታዊነትን፣ የሌሎችን ሃሳብ ማዳመጥንና ከሌሎች መማርን፣ መረዳዳትን፣ መተጋገዝን፣ የሃገር ፍቅርን &#8230; ወዘተ ባህሪያቸውና የሕልውናቸው አካል እንዲያደርጉ፤ በአንፃሩ ተንኮልን፣ ክፋትን፣ ግትርነትን፣ ቂመኛነትን፣ መጠላለፍን፣ ሰው መናቅን፣ እና የመሳለሉ የመንፈስ እድፎችን እንዲጠሉና እንዲያስወግዱ በማድረግ ልጆቻቸውን የእውነት “ሰው” አድርጎ የመቅረጽ ኃላፊነት አለባቸው። የሕፃንነት ዘመናቸው የነገ ማንነታቸው ፈጣሪና መሠረት ነውና።</p>
<p>ከዚህ አኳያ በወያኔ ጊዜስ? ቤተሰብ ይህንን ኃላፊነት በሚገባ እየተወጣ ነውን? መልሱ : “አይደለም” ነው። በዚህ ወቅት ለልጆች የመልካም ስብዕና ባለቤት መሆን መጨነቅ በሌላ አንገብጋቢ ጭንቀት ተተክቷል። በልቶ በማደር!!! ልጆቼ ምን በልተው፣ ምን ለብሰው፣ ምን ጠጥተው ትምህርት ቤት ይሂዱ? ከቤት ወጥተው ይዋሉ እንጂ ምን ሥነምግባር ተላበሱ የቅንጦት ጥያቄ ሆኗል። ሆዱ ያልሞላ ቤተሰብ ስለልጅ አስተዳደግ እንደምን ሊጨነቀው ይችላል? ይህ ከሆነ “የምትለብሰው የላት የምትከናነበው አማራት” ዓይነት ቅሌት ይመስላል። የሚላስ የሚቀመስ እየጠፋ ሕፃናት በየትምህርት ቤቱ በምግብ እጥረት ምክንያት ክፍል ውስጥ በሚወድቁበት አገር ቤተሰብ ቤቱ ከእጅ ወደአፍ በሆነ ኑሮ ሕይወቱን ማሳደር የሚችልበትን መላ ከማሰላሰል ባለፈ የልጆች ሥነምግባርና ሃገር ተረካቢነት ጉዳይ ከቶ እንዴት ሊታሰብ ይችላል? በፍጹም አይቻልም!!ቤተሰብ በችግር፣ በነፃነትና ተስፋ ማጣት ተወጥሯል። ስለሆነም አብዛኛው ኢትዮጵያዊ ቤተሰብ ውስጥ ያለ ልጅ አናጭ እና ቀራጭ አሮበት ሲባዝን ይውላል።</p>
<p><strong>2. የሃይማኖት ተቋማ</strong>ት</p>
<p>በእኔ እምነት ሁሉም ሃይማኖቶች መልካምና በመንፈስ የበለፀገ ትውልድን ለማፍራት የሚያስችል አስተምሮት አላቸው ። ምክንያቱን ሁሉም ሃይማኖቶች ልዕለ ኃያል የሆነ ተፈጥሮ ያላቸው ቸር፣ ሩህሩህ፣ አዛኝ፣ ቀና፣ ሁሉንም እኩል የሚያይ፣ ተንኮልንና ክፋትን የሚጠላ፣ጠጭነትን፣ ሴሰኝነትን፣ ቦዘኔነትን የማይወዱ ወዘተ ፈጣሪ ወይም ጌታ ወይም አምላክ ወይም መሲህ አላቸውና ። አስተምሮታቸውም በእነዚህ የመንፈስ ማጽጃ ጉዳዮችና ሌሎች ቀኖናዎች ላይ የተመሠረቱ ናቸው። በየሃይማኖቱ ጌቶች ወይም አምላኮች ወይም መላዕክት ወይም መሲሆች መልካም ባህሪዎች ተከታዩን ለመቅረጽ ይሞክራሉ።</p>
<p>በወያኔ ጊዜስ? &#8230; ከ1983 ዓም ወዲህ የሃይማኖት ተቋማት በየሃይማኖቱ ካህናትና መሪዎች ልብስ ባጌጡና በደመቁ፣ ቆብ በደፉ፣ መቁጠሪያ ባንጠለጠሉና ሻሽ በጠመጠሙ ካድሬዎች ተጥለቀለቁ። እንደ ፓለቲካው መዋቅሩና ሲቪል ቢሮክራሲው ሁሉ ተቋማቱ የዘመዳሞች መፈንጫ የጎጠኞች መራገጫ ሆኑ። የሃይማኖቱን ተከታይ መስበኪያ መድረኮች ከወያኔ የፕሮፖጋንዳ መለፈፊያ አደባባዮች፣ ቢሮዎችና ሚዲያዎች አልለይ አሉ። ቤተክርስቲያንና ቤተመንግሥትን ለመለየት ከቤቶች አናት ላይ የተሰቀለ መስቀልን መፈለግ የግድ ሆነ። ቤተመስጊድንና የፕሮፖጋንዳ ጽ/ቤቶችን ለመለየት ጨረቃንና ኮከብን ማማተር ወቅቱ የግድ አለ። ባጠቃላይ ድሎትንና ምቾትን በሚያሳድዱ የሃይማኖት መሪ ተብየዎች ተቋማቱ ተወረሩ። በመሆኑም ሌሎች ሁኔታዎች ከፈጠሩት ተስፋ መቁረጥ ጋር ተዳምሮ ትውልዱ ከሃይማኖት ተቋማት ሸሸ። የሃይማኖት ቤቶችን ጠላ። የሃይማኖት አባቶች ራቀ። ስለሆነም ከሥነምግባር ትምህርቶች ራቀ።</p>
<p><strong>3. ትምህርት ቤቶች</strong></p>
<p>ትምህርት ቤቶች የአንድ አገር ሕልውና ከሚወስኑ ጉዳዮች ዋነኛ የሆነውን ትምህርትና የተማረ ትውልድ መፍጠሪያ ተቋማት ናቸው። ደረጃቸውን የጠበቁ ትምህርት ቤቶች ደረጃቸውን ከጠበቁ መምህራንና የመማር ማስተማር ሁኔታ ጋር ሲደመሩ ትውልዱን በእውቀት ለማነጽ ዋናዎቹ ቦታዎች ናቸው። ነፃ ትምህርት ቤቶች፣ ነፃ የመማር ማስተማር ሂደት፣ነፃ መምህራን ከትክክለኛ የትምህርት ካሪኩለም ጋር ሲገናኑ በትክክልም ሰው መፍጠር ይቻላል።</p>
<p>በወያኔ ጊዜስ? &#8230; ግራ የገባው የትምህርት ካሪኩለም ትውልዱን ግራ እያጋባው ይገኛል። ትምህርት ቤቶች ልክ እንደ ሃይማኖት ተቋማት ሁሉ በወያኔ ካድሬዎች ተሞሉ፤ በወያኔ ካድሬዎች ተመሩ። ተማሪ ለወያኔ ስብሰባ ክፍል አቋርጦ የሚወጣበት ጊዜ መጣ። መምህራን በዘራቸው፣ በቋንቋቸው፣ በፓለቲካ አቋማቸውና በአጠቃላይ በማንነታቸእው የተነሳ ተዋከቡ። የትምህርት ቤቶች ንጹህ አየር ተበከለ። ትምህርት ቤቶች የእውቀት መቅሰሚያ ሳይሆኑ የጊዜ ማሳለፊያ ወይም መሸማቀቂያ ተቋማ ሆኑ። የአንደኛ ደረጃ፣ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እና ዩኒቨርስቲዎች የካድሬዎች የፓለቲካ ት/ቤት መሰሉ ። በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ኮሌጅ ና በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ መካከል ያለው ልዩነት በከተማው ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች መገኘታቸው ብቻ ሆነ። በመሆኑም ፕሮፌሰር ጌታቸውሃይሌ እንዳሉት ‘’አጼ ዘርዓ ያዕቆብ ማን እንደሆኑ የማያውቅ የኮሌጅ ተማሪ ያውም የደብረብርሃን ልጅ’’ ተፈጠረ:: ዩኒቨርስቲዎች የብሔር ግጭቶች ማሳያ ትያትር ቤቶች ሆኑ። የአካዳሚ ነፃነት ጠፍቶ፤ መምህራን የሚያውቁትን ማሳወቅ ቀርቶ የሚቀጥለውን ወር ደመወዛቸውን ስለመውሰዳቸው እርግጠኛ መሆን ተስኗቸው “መምህሩን ያጣ ሃገር ጭንቅላቱን ያጣ ሃገር” እንዳለው” ሎሬቱ ትውልዱ ያለ ጭንቅላት እየቀረ ነው።<br />
<strong></strong></p>
<p><strong>4. ማኅበረሰቡ</strong></p>
<p>በማኅበረሰቡ ውስጥ በረዥም የጊዜ ሂደት የሚፈጠሩ የጋራ እሴቶች፣ ባህሎች እና ማንነቶች ትውልድን ለማነጽ እጅግ ወሳኝ ናቸው። እነዚህ የትክክለኛነትና ስህተትነት ህጎች ከሌሎች ከተፃፉ መደበኛ ህጎች በበለጠ ኃያል ሲሆኑ የትውልዱን ማንነት በመቅረጹ በኩልም ያላቸው ኃይል ከፍተኛ ነው።</p>
<p>በወያኔ ጊዜስ?&#8230; ለወገን የመቆርቆር አልፎም ለሃገር የመሞት የሕዝቡ እሴቶች በፍርሃት በጥርጣሬና በጎመን በጤና አስተሳሰብ ተተኩ። መለያችን የነበረው ማኅበረሰባዊ ብልህነት ወደ ብልጠት ተቀየረ። ግለሰበኝነት፣ ሃሜት፣ ወሬ፣ ኢምክንያታዊነት አልፎ አልፎም ጥላቻ መልካም እሴቶቻችን እያጠፉ ይገኛሉ። ማኅበረሰቡ በአንድ ለአምስት አደረጃጀት ታስሮ እናት ልጇን ማመን የማትችልበት ዘመን መጣ፤ ጎረቤት ጎረቤቱን ማመን ተሳነው፤ እድሮች፣ እቁቦች፣ ሰንበቴዎችና ሌሎች ማኅበረሰባዊ መሰባሰቢያዎች የወያኔን የስለላ ተቋማት ያህል ማስፈራት ጀመሩ። ፍርሃትና ጥርጣሬ፤ ጥሎ ማለፍና ብልጠት የኑሮ ዘዴዎች ሆኑ።”ሃገር ማለት የእለት እንጀራ ሃይማኖት ማለት ለመሶብ መስገድ ሆነ”::</p>
<p><strong>5. ሲቪክ ተቋማት</strong></p>
<p>እነዚህ ሙያን፣ እድሜን ጾታን፣ ፍላጎትን ወይም ሌላ መስፈርትን መሠረት አድርጎ በተለይ በወጣቱ ትውልድ የሚመሠረቱ ተቋማት ወጣቱን እርስ በእርስ በማቀራረብ የጋራ ፍላጎቱን በጋር እንዲያንፀባርቅ በማድረግ፣ በጋራ ለጋራ ዓላማ መታገልን በማለማመድ፣ የዲሞክራሲ እሴቶችን የመለማመጃና የማስረጫ እድል በመክፈት፣ አባላት እርስ በርሳቸው አባላት የተቋማትን አመራር በአጠቃላይም ድርጅቱን የማመን ባህልን በማዳበር የሚጫወቱት ሚና ጉልህ ነው።</p>
<p>በወያኔ ጊዜስ? &#8230; ሲጀመር እንዲህ ዓይነት ትውልዳዊ ፋይዳ ያላቸውና ትውልዱን የዘመን ተሻጋሪ የራዕይ ባለቤት የሚያደርጉ፣ የሚያቀራርቡ፣ የሚያዋድዱ፣ማኅበረሰባዊ መተማመንን የሚፈጥሩ ተቋማት እንዲኖሩ አይፈለግም። ከ1983 ዓም በፊት የተመሠረቱ ቢሆንም እንኳን ከወያኔ የዘር ፓለቲካ እና የወኔ ቢስ ትውልድ ፈጣራ መርሃ ግብር ጋር እንዲጣጣሙ ሆነው ተስተካክለዋል። አዲስ የተፈጠሩትም በዚህ ማዕቀፍ ውስጥ ታስረው ተጥለዋል። ከቀበሌ እስከ ሃገር አቀፍ ደረጃ ድረስ በሥርዓቱ አባሎች እንዲመሩ ሁነው ሲቪካዊ ዓላማቸውን በመጣል የሥርዓቱ ጉዳይ አስፈፃሚዎች ሆነዋል። ስለሆነም ከዚህ አካባቢ ይገኝ ይገባው የነበር ትሩፋት ውሃ በልቶታል።</p>
<p><strong>6. የኢኮኖሚ ሥርዓት</strong></p>
<p>በአንድ አገር ውስጥ የተዘረጋ የኢኮኖሚ ሥርዓት በአገሪቱ የኢኮኖሚ እድገትና ሁለንተናዊ ለውጥ ላይ ካለው ቀጥተኛ ተጽዕኖ ባሻገር በወቅቱ ትውልድ ሥነምግባር ላይም ራሱ ሥርዓቱ ከፍተኛ ተጽዕኖ ይፈጥራል። በተለይ የኢኮኖሚ ሥርዓቱ በነፃ ገበያ የሚመራ ከሆነ በገበያው ውስጥ የሚኖረው ውድድር ሁሌም ፍትሃዊ ውድድርን፣ ለደንበኛ አያያዝ መጨነቅን፣ ለአገልግሎት ጥራት ከፍተኛ ትኩረት መስጠትን &#8230; ወዘተ መልካም የገበያ ባህሪያትን በትልቁ ግምት ውስጥ ያስገባ ነው። በነፃ ገበያ ውስጥ ግብይትና አጠቃላይ እንቅስቃሴው ሥርዓት ያለው፣ የውድድር ሥነምግባርን የተላበሰና የተረጋጋ ይሆናል። ይህ በአቋራጭና በብልጠት ሳይሆን በፍትሃዊ ውድድር ማሸነፍን ለትውልዱ ያስተምራል። በአንፃሩ ገበያው በጥቂቶች ቁጥጥር ውስጥ ወድቆ የውስን ሞኖፖሊዎች መፈንጫ ከሆነ አጠቃላይ እንቅስቃሴ ሁሉ ኢፍትሃዊ፣ ለደንበኛና ለጥራት እንዲሁም ለአገልግሎት የማይጨነቅ ይሆናል። ገበያው በጥቂቶች ቁጥጥር ሥር ይሆንና ደንበኞች ጥራት በሌለው ምርትና አገልግሎት ይስተናገዳሉ። ሥርዓቱም የተረጋጋ ግብረገብ ያለው አይሆንም።</p>
<p>በወያኔ ጊዜስ? &#8230; የፓለቲካና የኢኮኖሚ ሥርዓቱ ተቀላቅሎ የፓለቲካ ድርጅቶች ከንግድ ድርጅቶች መለየት ያስቸገረበት ጊዜ ነው። ተዋናይ ግለሰቦችም እንዲሁ ፓለቲከኛም፣ ባለሥልጣንም፣ ነጋዴም፣ ኮንትሮባንዲስትም፣ ጉቦኛም በሆኑባትና የማዘናጊያ ወይም የውሸት የነፃ ገበያ ሥርዓት በነገሰበት የወያኔ ሥርዓት ውጥንቅጡ እጅግ ሰፊና ምላሸ-ብዙ ይሆናል። በዚህ ሁኔታ ውስጥ እንደ ኤፈርት ዓይነት ያንድ ፓለቲካ ቡድን የንግድ ድርጅቶች ያለፍትሃዊ ውድድር፣ያለምንም ገደብ የግሉን ክፍለ ኢኮኖሚ ከጥቅም ውጭ ሲያደርጉት ይታያል። የእነዚህ ድርጅቶት መሪዎች የፓለቲካ መሪዎች ሆነው ስናይ፤ የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ባለሥልጣናት ትላልቅ የሙስና ወንጀል ውስጥ ተዘፍቀው ሲዋኙ ስናይ እና ጫት ነጋዴ ባለሥልጣናት በፈሉበት ዘመን ትውልዱ የሚማረው ከቶ ምን ሊሆን ይችላል? ካለውድድር መክበርን፤ በአቋራጭ መበልጸግን፣ ኪራይ ሰብሳቢነትን፣ ሙሰኝነትን፣ ብልጠትን፣ ተንኮልን &#8230; ወዘተ ካልሆነ በስተቀር። በአናቱ ድህነትና ኢፍትሃዊ የሃብት ክፍፍል ሲጨመርበት መዘዙ የከፋ ይሆናል። የወያኔዋ ኢትዮጵያ ሰዎች በዘራቸውና በፓለቲካ ድጋፋቸው ምክንያት በሁለት ቀን ፎቅ ዘርተው የሚያበቅሉባት አገር ሆናለች።</p>
<p><strong>7. የፓለቲካው ሥርዓት</strong></p>
<p>የፓለቲካ ሥርዓቶች (የመንግሥት ሥርዓቶች) በተፈጠሩበት አካባቢ እና ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ላልታወቀ ጊዜ ለሚቀጥሉ መልካምም ሆነ መጥፎ ክስተቶችና አሻራዎቻቸው ቀጥታ ተጠያቂ ናቸው።</p>
<p>የወያኔ ሥርዓት እንደ አንድ ሥርዓት በሀገሪቱ ውስጥ የተፈጠረው እጅግ አደገኛ የተንሸዋረረ አካሄድ እና እያስከተላቸው ያሉ ውጤቶች ከዚህ ጋር ተያይዞ የሚታይ ነው። የወያኔ ብሔር ተኮር ፋሺዝም ከላይ በ5 ንዑስ ርዕሶች ሥር ለመጥቀስ ከተሞከሩ ጉዳዮች እስከ ለጊዜው ያልተገለጡልን ምስቅልቅሎች ተጠያቂ ነው። ሥርዓቱ ባህሪው ያደረጋቸው ዘረኝነት፣ ስርቆት፣ ዝርፊያ፣ ጨለምተኝነት፣ አውዳሚነት፣ ራዕይ አልባነት፣ ካልበላልኝ የፊት ጥርሴ ይርገፍ ባይነት፣ እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል ባህሪይ፣ ቡድንተኝነት፣ ጎጠኝነት፣ ጥላቻ፣ ቂም በቀል፣ ጥርጣሬ፣ አለመተማመን፣ ጥሎ ማለፍ ወዘተ በትውልዱ ላይ ጥቁር ጥላቸውን እያጠሉ ነው። ለትውልዱ ተስፋን የሚተልም ሥርዓት ጠፋ። ሞዴል የሚሆን የፓለቲካ (የመንግሥት) አመራር ማግኘት ሕልም ሆነ።</p>
<p>ታድያ ቤተሰብ፣ ማኅበረሰብ፣ ት/ቤቶች፣ የሃይማኖት ተቋማት፣ ሲቪክ ተቋማት የፓለቲካ ሥርዓቱ የእኔን ትውልድ በሥርዓቱ አንጾ ኃላፊነት መሸከም የሚችል እና ነገን በራዕይ፣ በተስፋ የሚያይ ማድረግ ካልቻሉ ትውልዱ የት ሄዶ ግብረገብነትን፣ ራዕይተኝነትን፣ ታላቅነትን ይማር? መቼ? እንዴት?</p>
<p>የእኔ ትውልድ እየናወዘ ነው። የእኔ ትውልድ ወኔው እየሞተ ተስፋው እየሟሸሸ፣ እየደነዘዘ ነው። ነገ የሚባል የተፈጥሮ ሥርዓት መኖሩንም እየረሳ ነው። ባለራዕይ መሆን ቅሌት ራስን ለትልቅ ቦታ እና ለሀገር ኃላፊነት ማጨት እብደት እየመሰለ ነው ። ይኸን ለማለትና ለመገንዘብ ጠቢብ መሆን አይጠይቅም &#8211; ኢትዮጵያ ውስጥ መኖር ይበቃል።</p>
<p>ለዚህ በርካታ ምሳሌዎችን ማንሳት ቢቻልም ጥቂቶቹን ብቻ ለማሳየት ልሞክር</p>
<p><strong>i. ጫት፣ መጠጥና ኤች አይ ቪ ኤድስ</strong></p>
<p>እስቲ ለደቂቃ ቆም ብለን እናስብ። ምን ያህል ወጣትና ጎልማሳ ነው በዛሬው ጊዜ የማይጠጣና የማይቅም? ጫት ከዚህ በፊት በስፋት ከሚታወቅባቸው ቦታዎች አልፎ ስሙ እንኳን እንደ ሳጥናኤል ያስፈራባቸው በነበሩ የአገራችን ሰሜናዊ ክፍሎች ወጣቱ ያለጫት መዋል እየከበደው ነው። ባህርዳር፣ ጎንደር፣ ደብረ ማርቆስ፣ ወልዲያ፣ ደሴ፣ መቀሌ &#8230; ወዘተ ለአንድ ቀን ጫት ቢጠፋ ብጥብጥ ይፈጠራል። በእኔ እምነት ጫት መቃምን ያወግዝ የነበረ “ጨዋ” ነኝ የሚል ማኅበረሰብ ልጆች ጫት ቤት የመከተም ምክንያት የኔ ትውልድ የመንፈስ መድቀቅና የሞራል መላሸቅ ነው። ከዚህ ሌላ ምን ሊሆን ይችላል? ምናልባት መቃሙ፣ መጠጣቱ ወደሌላ የተስፋ መቁረጥ አዙሪት ውስጥ ይከተው ይሆናል። መቃም ካለ መጠጣት ይከተላል። መቃምና መጠጣት ካለ ወሲብ ይኖራል &#8211; ያውም ሊቅ ወሲብ። ሊቅ ወሲብ ካለ ኤች አይ ቪ ኤድስ አለ። እዚህ ላይ የኤች አይ ቪ ኤድስ የስርጭት መጠን በ 2002 ዓም 15 % የደረሰበት የአገራችን ከተማ አለ ብል አንዳንዶች ሊገረሙ ይችላሉ። መገረም ግን አያስፈልግም። የሞራል ዝቅጠትና መዘዙ መለኪያ ኖሮት ቢለካ ወይም ማሳያዎች በጥንቃቄ ቢጠኑ አስደንጋጭ ውጤቶችን እናገኛለን። ይህ ባለ 15% ከተማ ጫት በብዛት ከሚቃምባቸው ከተሞች አንዱ ነው። ትውልዱ የእኔ ነው የሚለው አንድም ነገር አጣ። ነገ እንደሰማይ ራቀችው። ስለሆነም ጫትቤት ተደብቆ ብትመጪም ለራስሽ ብትቀሪም ጉዳይሽ እያላት ይገኛል። በምርቃና ትዝ ስትለው በመጠጥ ይረሳታል። ስካሩ ሲለቀው ደጋግማ እየተከሰተች እንዳትረብሸው በበሽታ ይገላገላታል።</p>
<p>ተማሪዎች ከትምህርት ቤቶች ይልቅ ጫት ቤቶችን መርጠዋል። የመንግሥትና የፓለቲካ ተቋማት ቢሮዎች ሰራተኛ ቁጥር ከምሳ ሰዓት በኋላ ቢያንስ በግማሽ ይቀንሳል። ባለሥልጣኖች አዳዲስ ሞዴል መኪናዎቻቸውን ሸራ አልብሰው በልጃገረዶች ታጅበው ሺሻቸውን እያንደቀደቁ ጫት ሲያመነዥኩ ይውላሉ። ይህን ምን ይሉታል?</p>
<p><strong>ii. ማኅበራዊ ሴሰኝነት</strong></p>
<p>በኢትዮጵያ ሁኔታ እንደ ወያኔ ዘመን ማኅበራዊ ሴሰኝነት ነግሶ ልቅ የወሲብ ስሜት ትውልድን ለቁም ገዝቶ የሚያውቅበት ጊዜ ያለ አይመስለኝም። ወጣቱ በአንድ መወሰንን የኋላቀርነት (“የፋራነት”) መገለጫ አድርጎታል። በአንድ ቀን ከሶስትና ከዚያ በላይ ሴቶች ጋር የወሲብ ግኑኝነት መፈፀም የአሪፍነት መለኪያ ከሆነ ሰነባብቷል። በአጠቃላይ ትምህርት ቤቱ፣ የመንግሥት ተቋሙ፣ ከተማው፣ ገጠሩ፣ በሙሉ አገሩ ሴሰኝነት ሴሰኝነት ሸቷል። የዚህ ትዕይንት ግንባር ቀደም ተዋንያን ደግሞ የመንንግሥት ባለሥልጣናት ናቸው። ባለሥልጣናቱ ከሕዝብ በዘረፉት ገንዘብ የሕዝብን ልጆች ያማግጡበታል። በግሌ በዚህ ድርጊት ውስጥ የማውቃቸው ከፍተኛ ባለሥልጣናት ብዙ ናቸው። ከቡናቤት ሴቶች ዘለው በየሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶቸና ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ በደላላ ሴት ሲያስመለምሉ ይውላሉ። ከዘረፉት ገንዘብ አፍሰው ያሸክማሉ። ስለሆነም ለጋ ሕፃናት እህቶቻችን የንዋይ ውድድር ውስጥ ይገባሉ። በዚህም ምክንያት ዩኒቨርስቲዎችና ኮሌጆች ያሉባቸው የኢትዮጵያ ከተሞች ውስጥ የእህቶቻችን ስም ዝርዝር ከነ ፎቶዓቸውና የስልክ አድራሻ ያካተተ ማውጫ በየሆቴሉ ውስጥ ተቀምጦ ያገኛሉ። እርስዎ መርጠው መደወል ወይም ማስደወል ነው። ይህንንስ ምን ይሉታል?</p>
<p>በኢትዮጵያ በሚገኝ አንድ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ውስጥ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ በአንድ የግል ክሊኒክ ብቻ 300 ሴት ተማሪዎች ጽንስ አስወርደዋል። ይህንንስ ምን እንበለው?</p>
<p>ማኅበራዊ ሴሰኝነት የሚባል በሽታ ለክፎን ከነሰቆቃችን እያሳቀና እያስደሰተ እየገደለን ነው።</p>
<p><strong>iii. ስደት</strong></p>
<p>ወጣቱ ሞት በፊት ለፊቱ እንደ ጅብራ ተገትሮ ተመለስ እያለው እንቢ ብሎ እየተሰደደ ነው። ኢትዮጵያ ውስጥ ከመኖር “ሜደተራንያን ውስጥ ልስመጥ፤ የውስጥ አካሌ ይሸጥ፤ ከፎቅ ልወርወር፤ በቡድን ልደፈር፤ በፈላ ውሃ ልቀቀል፤ ሠሃራ ይብላኝ” እያለ የሚሰደደው ገንዘብ ፍለጋ አይመስለኝም በሀገሩ ያጣውን ተስፋና ራዕይ ፍለጋ እንጂ።</p>
<p><strong>iv. ውሸትና ብልጠት</strong></p>
<p>ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይዋሻል። ፓርላማው ይዋሻል። ቴሌቪዥኑ ቀን ተሌት ይዋሻል። ትንሹ ትልቁ ይዋሻል። ምድሪቱ የውሸት ምድር ሆነች። እውነት መናገር እና ብልህነት ሞኝነት ሆነ። ውሸትና ብልጠት ብልህነት ሆነ። አዋቂና ብልሆች በብልጦችና ውሸታሞች ማኅበረሰባዊ ሚናቸውን ተነጠቁ:: የውሸት መማር፤ የውሸት መቆፈር፤ የውሸት መሳቅ፤ የውሸት መናገር፤ የውሸት ሪፖርት፤ የውሸት ስብዕና፤ የውሸት መኖር፤ ባጠቃላይ ዛሬን የውሸት አደረጉት። ዛሬ የውሸት ሁኖ ነገ እውነት አትሆንም። “የውሸት እየሠሩ፤ የእውነት መብላት” ወንዝ አያሻግርም።</p>
<p>እነዚህ ጥቂት ማሳያዎች ናቸው። በእኔ የግንዛቤ አድማስ የተወሰኑ ናቸው። የእድሜ እና የእውቀት ታላላቆቼ ከዚህ የባሰ እና አስፈሪ የትውልድ መበስበስ ሊታያቸው እንደሚችል እርግጠኛ ነኝ።</p>
<p><strong>8. መፍትሔ</strong></p>
<p>በእኔ እምነት የእዚህ ሁሉ ችግሮች መፍትሔ አንድ ነው፦ ለእነዚህ ሁሉ ችግሮች መፈጠርና መባባስ ምክንያት የሆነውን ወያኔን በፍጥነት ማስወገድ ዋናውና የመጀመሪያው ነው። ስርአቱን ለማስወገድ ሲሞከሩ የቆዩ የተለያዩ የትግል ስልቶች በግልጽ እያሳዩት የመጡት ጉዳይ ቢኖር ወያኔን በፍጥነት ማስወገድ የሚቻለው ህዝባዊ እንቢተኝነትን አና የመሳሪያ ትግልን ባጣመረ ሁለገብ የትግል ስልት ነው :: ወያኔን ማስወገድ ብቸኛው እና የመጨረሻው መፍትሄ ሊሆን ግን አይችልም:: ይልቁንም በህዝብ ነጻ ፍላጎት ወደ ስልጣን በመጣ የፖለቲካ ስርአት መተካት ያስፈልጋል:: ስለዚህ በህዝብ የተመረጠ እና ለህዝብ ቅድሚያ የሚሰጥ ስርአትን መፍጠር ሁለተኛው ወሳኝ ምእራፍ ነው:: እንዲህ ሲቀርብ ታዲያ ቀላል ይመስላል:: ከእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ በተለይ ደግሞ ራሳቸውን ካደራጁ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና ተቆርቋሪዎች እጅ ተሰርቶ እንዲቀርብ የሚጠበቀው የቤት ስራ እጅግ ከባድ እና ውስብስብ ነው:: ከላይ የተዘረዘሩ ሃቆች ባለቤት የሆነ ሃገር እና ትውልድ ተሸክመን፣ አሳዛኝ ወቅት ውስጥ ቆመን የምንመኘውን በዴሞክራሲያዊ ስርአት ላይ የቆመ ነፃ ሃገርና ነፃ ህዝብ ማየት፣ ማግኘት፣ መኖርና መሆን የምንችለው ከችግሩ ፊት በድፍረት መቆም እና መጋፈጥ አልፎም መፍትሄ አፍላቂ የሆኑ ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር ስንችል ብቻ ነው:: የምንፈጥረው ዴሞክራሲያዊ ስርአት የሚተከልበት ብሎም ለዘመናት ተጠብቆ የሚቆምበትና የሚፋፋበት ለም መሬት የመፍጠር ጉዳይ ምን ያህል አስቸጋሪ እንደሆነ እንዳላየን ተሸፋፍነን የምናልፈው/የምንሻገረው/ ጉዳይ አይደለም:: ጠንካራና ነጻ ተቋማትንና የምንመኘውን ሁሉንም ኢትዮጵያዊ በእኩል የሚያሳትፍ የሁላችን የሆነ ዴሞክራሲያዊ ስርአትና ሃገር ለመገንባት ከራሱ ጋር የታረቀ፣መንፈሰ ጠንካራ፣የነቃና፣ለነገ የሚጓጓ ማህበረሰብ በተለይ ወጣት ትውልድ ያስፈልጋል::ይህ ሲሆን ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት መፈጠር ምቹ መደላድል አስቀመጥን ማለት ነው:: እዚህ ደረጃ ላይ ቆሞም ዘላቂ የሆነ የባህል ህዳሴን እና ማህበራዊ አብረሆትን መመኘትም ማሳካትም ይቻላል:: የግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይል ወያኔን በመሳሪያ ትግል ማስወገድ የመጀመሪያው ዋና ምእራፍ ነው ብሎ ሲነሳ ለሁለተኛው ምእራፍ መፈጠር የሚያስፈልገው ዋናው ቅድመ ሁኔታ ያስጨንቀዋል:: ሰው::!!! ራዕይ ያለው ነገን በተስፋ የሚያይ ሰው::!! የዴሞክራሲንና ነፃነትን ትርጉም የተረዳ ና በውስጡ ያሰረጸ ወጣት ትውልድ::!!!! ስለሆነም ወያኔ የዘመኑ ትወልድ ላይ እየፈጠረ ያለው የመንፈስ ድቀት እና ልሽቀት ሁሉም ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ ለሰከንዶች ሊዘናጋበት የማይገባ የዴሞክራሲ ስርዓት ምስረታችን ፈተና መሆኑን በጥልቅ መገንዘብ በእጂጉ ያስፈልጋል:: በመሆኑም የወጣት ምሁራንን ትኩስ አቅም ከሀገሪቱ አንጋፋ ፖለቲከኞች የዘመናት የትግል ተሞክሮ ጋር በማዋሃድ ተመስርቶ የሚመራው ድርጅታችን ተዋጊ ብቻ ሳይሆን ለዴሞክራሲያዊ ስርአት መፈጠርና በዘላቂነት መቀጠል እንዲሁም ለህዝባችን ሁለንተናዊ ለውጥ እርሾና አጋዥ የሚሆን ብቁ የሆነ የሰው ሀይል የመፍጠር ጉዳይ ያሳስበዋል:: አቅዶ ይሰራበታል:: እየሰራበትም ይገኛል:: ስለሆነም ለጋራ ሃገራችን እጣ እና መጭ ተስፋ በዚህ ረገድ በጋራ በመስራትና በመነቃነቅ የትግሉን እድሜ ማሳጠር ብሎም የትግሉን ውጤት ማሳመር ይኖርብናል:: ለዚህም ብዙ ይጠበቃል:: በጋራ በጽናት መቆም ይኖርብናል: ይህን ማድረግ ከቻልን በጋራ፣ ለጋራ የሚሆን አጓጊ ነገን መፍጠር እንችላለን።</p>
]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ginbot7.org/2013/05/02/%e1%8b%a8%e1%8b%98%e1%88%98%e1%8a%91-%e1%89%b5%e1%8b%8d%e1%88%8d%e1%8b%b5-%e1%88%a5%e1%8a%90-%e1%88%9d%e1%8c%8d%e1%89%a3%e1%88%ad-%e1%8b%88%e1%8b%b4%e1%89%b5/feed/</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>በአፋር ክልል የሚኖሩ የትግራይ ተወላጆች የሚኖሩበትን ቦታ እኛዉ እናስተዳድዉ የሚል ጥያቄ ማቅረባቸዉ ተሰማ</title>
		<link>http://www.ginbot7.org/2013/04/29/%e1%89%a0%e1%8a%a0%e1%8d%8b%e1%88%ad-%e1%8a%ad%e1%88%8d%e1%88%8d-%e1%8b%a8%e1%88%9a%e1%8a%96%e1%88%a9-%e1%8b%a8%e1%89%b5%e1%8c%8d%e1%88%ab%e1%8b%ad-%e1%89%b0%e1%8b%88%e1%88%8b%e1%8c%86%e1%89%bd/</link>
		<comments>http://www.ginbot7.org/2013/04/29/%e1%89%a0%e1%8a%a0%e1%8d%8b%e1%88%ad-%e1%8a%ad%e1%88%8d%e1%88%8d-%e1%8b%a8%e1%88%9a%e1%8a%96%e1%88%a9-%e1%8b%a8%e1%89%b5%e1%8c%8d%e1%88%ab%e1%8b%ad-%e1%89%b0%e1%8b%88%e1%88%8b%e1%8c%86%e1%89%bd/#comments</comments>
		<pubDate>Mon, 29 Apr 2013 16:12:44 +0000</pubDate>
		<dc:creator>admin</dc:creator>
				<category><![CDATA[አማርኛ ዜናና መግለጫ]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.ginbot7.org/?p=5069</guid>
		<description><![CDATA[የአማራን ተወላጆች የገቡበት ቦታ ሁሉ እየገባ ወደ ክልላችሁ ሂዱ እያለና ንብረታቸዉን እየቀማ የሚያፈናቅለዉ የወያኔ አገዛዝ ታማኝ የሆኑ የትግራይ ተወላጆች አፋር ክልል ዉስጥ በብዛት ሰፍረዉ በሚገኙበት ቦታ እራሳችንን በራሳችን የማስተዳደር መብት የስጠን የሚል ጥያቄ ማቅረባቸዉን ከሰሞኑ ከወደ አፋር ክልል የነፈሰዉ ዜና አስረዳ። በአፋር ክልል የዞን ሁለት ዋና ከተማ በሆነችዉ አብአላ ዉስጥ የሚኖሬት ቁጥራቸዉ 15 ሺ የሚጠጋ [...]]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<p>የአማራን ተወላጆች የገቡበት ቦታ ሁሉ እየገባ ወደ ክልላችሁ ሂዱ እያለና ንብረታቸዉን እየቀማ የሚያፈናቅለዉ የወያኔ አገዛዝ ታማኝ የሆኑ የትግራይ ተወላጆች አፋር ክልል ዉስጥ በብዛት ሰፍረዉ በሚገኙበት ቦታ እራሳችንን በራሳችን የማስተዳደር መብት የስጠን የሚል ጥያቄ ማቅረባቸዉን ከሰሞኑ ከወደ አፋር ክልል የነፈሰዉ ዜና አስረዳ። በአፋር ክልል የዞን ሁለት ዋና ከተማ በሆነችዉ አብአላ ዉስጥ የሚኖሬት ቁጥራቸዉ 15 ሺ የሚጠጋ የትግራይ ተወላጆች ብዛት ስላለን እራሳችንን የማስተዳደር መብት ይሰጠን ሲሉ ያቀረቡትን ጥያቄ የክልሉ ሰብአዊ  መብቶች ሃለፊ የሆኑት አቶ ገአስ አህመድ አዎንታዊ መልስ የማያስፈልገዉና አግባብ የሌለዉ ተራ ጥያቄ ነዉ ሲሉ የትግራይ ተወላጆች ያቀረቡትን ጥያቄ አጣጥዉታል።</p>
<p>አቶ ጋአስ በዱብቲ ከተማ በርካታ የአማራ፣ የኦሮሞ እና የትግራይ ተወላጆች ቢኖርም አንድም ቀን የወረዳ ጥያቄ አለማንሳታቸውን ገልጸው፣ ከመቀሌ በ45 ኪሎሜትር ርቀት ላይ በሚገኘው አብአላም ከተማ የሚኖሩ የትግራይ ተወላጆች ያቀረቡት ጥያቄ  አሳዛኝ መሆኑን ገልጸዋል። የአፋር ክልል በህወሀት ሰዎች የሚመራ መሆኑን የገለጹት አቶ ገአስ፣ ተወላጆቹ ወረዳ ይሰጠን ከሚሉ ክልሉ የራሳቸው መሆኑን ቢያውቁት ይሻል ነበር ብለዋል። እንደ አቶ ገአስ አባባል አብላ ከተማ ዉስጥ የሚኖሩት የትግራይ ተወላጆች ከተማዋ በራሳቸዉ ቋንቋ ሸከት ተብላ እንድትጠራና እንዲሁም የአፋር ክልላዊ መንግስት በከተማዋ መሬት ለኢንቨስትመንት መስጠት አይችልም የሚሉ ጥያቄዎችን ማንሳታቸዉን ጠቅሰዉ በአሁኑ ጊዜ በአፋር ክልል የህወሀት ባለስልጣናት ግምገማ እያስደረጉና የራሳቸውን ሰዎች እየሾሙ ክልሉን ለውድመትና ለጥፋት እየዳጉት መሆናቸዉን ተናግረዋል።</p>
]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ginbot7.org/2013/04/29/%e1%89%a0%e1%8a%a0%e1%8d%8b%e1%88%ad-%e1%8a%ad%e1%88%8d%e1%88%8d-%e1%8b%a8%e1%88%9a%e1%8a%96%e1%88%a9-%e1%8b%a8%e1%89%b5%e1%8c%8d%e1%88%ab%e1%8b%ad-%e1%89%b0%e1%8b%88%e1%88%8b%e1%8c%86%e1%89%bd/feed/</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>የወያኔ ፖሊሶች ከግንቦት7 ህዝባዊ ኃይል ጋር ግንኙነት አለዉ የሚሉትን ወጣት ሁሉ እየከበቡ ማሰር ጀመሩ</title>
		<link>http://www.ginbot7.org/2013/04/29/%e1%8b%a8%e1%8b%88%e1%8b%ab%e1%8a%94-%e1%8d%96%e1%88%8a%e1%88%b6%e1%89%bd-%e1%8a%a8%e1%8c%8d%e1%8a%95%e1%89%a6%e1%89%b57-%e1%88%85%e1%8b%9d%e1%89%a3%e1%8b%8a-%e1%8a%83%e1%8b%ad%e1%88%8d-%e1%8c%8b/</link>
		<comments>http://www.ginbot7.org/2013/04/29/%e1%8b%a8%e1%8b%88%e1%8b%ab%e1%8a%94-%e1%8d%96%e1%88%8a%e1%88%b6%e1%89%bd-%e1%8a%a8%e1%8c%8d%e1%8a%95%e1%89%a6%e1%89%b57-%e1%88%85%e1%8b%9d%e1%89%a3%e1%8b%8a-%e1%8a%83%e1%8b%ad%e1%88%8d-%e1%8c%8b/#comments</comments>
		<pubDate>Mon, 29 Apr 2013 16:11:47 +0000</pubDate>
		<dc:creator>admin</dc:creator>
				<category><![CDATA[አማርኛ ዜናና መግለጫ]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.ginbot7.org/?p=5067</guid>
		<description><![CDATA[የዘረኛዉ ወያኔ የፖሊስና የጸጥታ ኃይሎች በቅርቡ እራሱን ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋራ ካስተዋወቀዉ ከግንቦት ሰባት ህዝባዊ ኃይል ጋር ግንኙነት አለዉ ብለዉ የሚጠረጥሩትን ወጣት እያደኑ ማሰር መጀመራቸዉን የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን ታማኝ የአገር ዉስጥ ምንጮቹን ዋቢ አድርጎ በዘገበዉ ዜና ገለጸ። ለኢሳት የደረሰው መረጃ መሠረት መሳሪያ አንግበዉ ከአዲስ አበባ በብዛት የተንቀሳቀሱ የፌደራል ፖሊስ አባላት ከባህርዳር በ35 ኪሜ ርቀት ላይ ወደምትገኘዉ [...]]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<p>የዘረኛዉ ወያኔ የፖሊስና የጸጥታ ኃይሎች  በቅርቡ እራሱን ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋራ ካስተዋወቀዉ ከግንቦት ሰባት ህዝባዊ ኃይል ጋር ግንኙነት አለዉ ብለዉ የሚጠረጥሩትን ወጣት እያደኑ ማሰር መጀመራቸዉን የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን ታማኝ የአገር ዉስጥ ምንጮቹን ዋቢ አድርጎ በዘገበዉ ዜና ገለጸ። ለኢሳት የደረሰው መረጃ መሠረት መሳሪያ አንግበዉ ከአዲስ አበባ በብዛት የተንቀሳቀሱ የፌደራል ፖሊስ አባላት ከባህርዳር በ35 ኪሜ ርቀት ላይ ወደምትገኘዉ መርአዊ የምትባል ከተማ በመሄድ ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎችን አፍነው አዲስ አበባ ዉስጥ ለግዜዉ ወዳልታወቀ ቦታ እንደወሰዷቸዉ ለማወቅ ተችሏል።</p>
<p>ምሽት ላይ አድፍጠዉ መርአዊ ከተማ የገቡት ፖሊሶችና የደህንነት ኃይሎች የአካባቢውን ሰዎች በማስፈራራት ተማሪዎቹን አፍነው የወሰዱዋቸው ሲሆን፣ በወቅቱ አንድ ወጣት ክፉኛ መደብደቡን ለማረጋጥ ተችሏል። አንድ የባህር ዳር ነዋሪ ለግንቦት ሰባት ዜና ዜና ዝግጅት ክፍል ስልክ ደዉለዉ የተማሪዎቹን መታሰርና መደብደብ ካወገዙ በኋላ የኢትዮጵያ ህዝብ አንቅሮ እንደተፋዉና ስርአቱን ለመደምሰስ በእንቅስቃሴ ላይ እንደሚገኝ የተረዳዉ ወያኔ የቀብፀ ተስፋ እርምጃ መዉሰዱ የሚገርም ባይሆንም አይኑ ያተፈበትንና ገደብ የሌለዉ እጁ የደረሰበትን ዜጋ ሁሉ እያፈሰ ማሰር መጀመሩ ህዝብ የጀመረዉን የፍትህ፤ የነጻነትና የደሞክራሲ ትግል አጠናክሮ የድሉን ግዜ ያፋጥነዋል እንጂ አያሳጥረዉም ብለዋል።</p>
<p>ይህ በእንዲህ እንዳለ በኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊት ውስጥ የደህንነት ሹም በመሆን ለረጅም ጊዜ ያገለገለዉ የሻለቃ መሳፍንት ጥጋቡ ወያኔን በመክዳት የግንቦት7 ህዝባዊ ሀይልን መቀላቀሉ ታውቋል። ሻለቃ መሳፍንት በመከላከያ ሰራዊት ውስጥ ስላለው የዘር ችግር፣ በብአዴን ውስጥ ስለሚነሱ ቅሬታዎች እና መሰል ጉዳዮች ዛሬ ከኢሳት ጋር ሰፊ ቃለምልልስ አድርጓል። ሙሉ ቃለምልልሱ በቅርቡ ይቀርባል።</p>
]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ginbot7.org/2013/04/29/%e1%8b%a8%e1%8b%88%e1%8b%ab%e1%8a%94-%e1%8d%96%e1%88%8a%e1%88%b6%e1%89%bd-%e1%8a%a8%e1%8c%8d%e1%8a%95%e1%89%a6%e1%89%b57-%e1%88%85%e1%8b%9d%e1%89%a3%e1%8b%8a-%e1%8a%83%e1%8b%ad%e1%88%8d-%e1%8c%8b/feed/</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>የጠ/ሚኒስትር ሀይለማርያም  ፓርላማ ዉሎ  የፓርላማዉን አባላት ጭምር ማስቆጣቱ ታወቀ</title>
		<link>http://www.ginbot7.org/2013/04/29/%e1%8b%a8%e1%8c%a0%e1%88%9a%e1%8a%92%e1%88%b5%e1%89%b5%e1%88%ad-%e1%88%80%e1%8b%ad%e1%88%88%e1%88%9b%e1%88%ad%e1%8b%ab%e1%88%9d-%e1%8d%93%e1%88%ad%e1%88%8b%e1%88%9b-%e1%8b%89%e1%88%8e-%e1%8b%a8/</link>
		<comments>http://www.ginbot7.org/2013/04/29/%e1%8b%a8%e1%8c%a0%e1%88%9a%e1%8a%92%e1%88%b5%e1%89%b5%e1%88%ad-%e1%88%80%e1%8b%ad%e1%88%88%e1%88%9b%e1%88%ad%e1%8b%ab%e1%88%9d-%e1%8d%93%e1%88%ad%e1%88%8b%e1%88%9b-%e1%8b%89%e1%88%8e-%e1%8b%a8/#comments</comments>
		<pubDate>Mon, 29 Apr 2013 16:10:32 +0000</pubDate>
		<dc:creator>admin</dc:creator>
				<category><![CDATA[አማርኛ ዜናና መግለጫ]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.ginbot7.org/?p=5065</guid>
		<description><![CDATA[የወያኔ ታማኝ ሎሌ የሆነዉ ጠ/ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ባለፈዉ ሳምንት የፓርላማ ዉሎዉ 40 በ 60 የተባለውን የቤቶች ልማት ፕሮጀክት አስመልክቶ ለቀረበለት ጥያቄ የሰጠዉ ምላሽ ከዚህ ቀደም ባልተለመደ መልኩ ከዚህ ቀደም ከሳቅና ጭብጨባ ዉጭ ሌላ መቃወም የሚባል ነገር የማያዉቀዉን የወያኔ ፓርላማ ማስቆጣቱ ተሰማ፡፡ ኃይለማርያም ደሳለኝ ይህ እንግዳ የሆነ ተቃዉሞ የገጠመዉ የ2005 በጀት ዓመት የስምንት ወራት ሪፖርት ባቀረበበት [...]]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<p>የወያኔ ታማኝ ሎሌ የሆነዉ ጠ/ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ባለፈዉ ሳምንት የፓርላማ ዉሎዉ 40 በ 60 የተባለውን የቤቶች ልማት ፕሮጀክት አስመልክቶ ለቀረበለት ጥያቄ የሰጠዉ ምላሽ ከዚህ ቀደም ባልተለመደ መልኩ ከዚህ ቀደም ከሳቅና ጭብጨባ ዉጭ ሌላ መቃወም የሚባል ነገር የማያዉቀዉን የወያኔ ፓርላማ ማስቆጣቱ ተሰማ፡፡ ኃይለማርያም ደሳለኝ ይህ እንግዳ የሆነ ተቃዉሞ የገጠመዉ የ2005 በጀት ዓመት የስምንት ወራት ሪፖርት ባቀረበበት ወቅት ሲሆን  የፓርላማዉ አባላት 40 በ 60 የሚባለው የቤት ልማት መቶ በመቶ የመክፈል አቅም ላላቸው ሰዎች ቅድሚያ ይሰጣል የመባሉን ጉዳይ እርግጠኛ ስለመሆኑ ለጠየቀዉ ጥያቄ አዎንታዊ መልስ በመስጠቱ ወይም  መቶ በመቶ የመክፈል አቅም ላላቸው ቅድሚያ እንደሚሰጥ በማረጋገጡ  ፓርላማዉ በተቃዉሞ ድምፅ ሲሞላ ተስተዉሏል።</p>
<p>ለወያኔ ፓርላማ ቅርበት ያላቸው ምንጮች የፓርላማዉ አባላት ለምን አለወትሯቸዉ ጠ/ሚኒስትር ኃ/ማሪያም ደሳለኝ ላይ እንዳልጎመጎሙ ተጠይቀው በሰጡት መልስ ቀደም ሲል ፕሮግራሙን በተመለከተ ለፓርላማው በቀረበዉ ሪፖርት 40 በ60 የሚባለው ፕሮግራም መካከለኛ ገቢ ያለውን በተለይም በደሞዝ የሚተዳደረውን የህብረተሰብ ክፍል ይጠቅማል ተብሎ መነገሩንና ሆኖም በዕቅድ ደረጃ  ለባለአንድ ክፍል መኝታ ቤት 857 ብር፣ለባለሁለት መኝታ ቤት 1 ሺ 337 ብር፣ ለባለሶስት ምኝታ ቤት ደግሞ 2 ሺ133 ብር ለአምስት ተከታታይ ዓመታት በየወሩ መቆጠብ እንዳለበት መታቀዱ የመካከኛ ገቢ ያለውን የህብረተሰብ ክፍል አቅም ያገናዘበ አይደለም የሚል ቅሬታ በፓርላመዉ አባላት ዘንድ በቅሬታ መልክ በተደጋጋሚ ይነሳ እንደነበረ አስታውሰዋል፡፡</p>
<p>በኢትዮጵያ ተጨባጭ ሁኔታ መካከለኛ ገቢ አለው የሚባለው በተለይም የመንግስት ሰራተኞች አማካይ ወርሃዊ መካከለኛ ገቢ ከ2 ሺ 500 ብር እንደማይበልጥ ምንጫችን ጠቅሶ ከዚህ ደመወዝ ላይ ዝቅተኛውን በወር 857 ብር መቆጠብ እንዴት ይቻላል ሲል የወያኔን ግራ የሚያጋባ አሰራር  ገና ሳይጀመር ጥያቄ ዉስጥ የገባ አሰራር ነዉ ብሎታል፡፡ በዚህ ምክንያት የ40 በ60 የቤት ልማት ፕሮግራም መካከለኛ ገቢ ላላቸዉ ሰዎች ይዘጋጅ እንጂ እካሁን ድረስ እየጠቀመ ያለዉ ከፍተኛ ገቢ ያላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ነዉ፤ ይህንን ደግሞ ኃ/ማሪያም ደሳለኝም ፓርላማ ዉስጥ ባደረገዉ ንግግር አረገግጦታል ብሏል፡፡</p>
<p>ይህ በእንዲህ እንዳለ  ጠ/ሚኒስተር ኃ/ማሪያም ደሳለኝ ቢሮ አማካይነት በተደረገው ጥናት ለውጪ ኩባንያዎች ዝግየሆነውን የሸቀጦች ችርቻሮ ንግድ ስራ ለመፍቀድ ወይ ሌሎች አማራጮችን ለማየት መሞከሩን የኢሳት ቴሌቭዥንና ሬድዮ ዘጋቢ ጠቅሶ ይህ ነገር ግን ትልልቆቹ ኩባንያዎች በሸቀጦች የችርቻሮ ንግድ እንዲሰማሩ ቢደረግ የአገር ውስጥ አስመጪዎች በአጭር ጊዜያት ውስጥ ከገበያ ውጪ በማድረግ መንግስት ሊቆጣጠረው የማይችለው ገበያ ሊፈጠር ይችላል የሚል ስጋት በመኖሩ በመንግስት ቁጥጥር ስር ሆኖ ዋጋ የማረጋጋትና አነስተኛ ዋጋ ካላቸው ገበያዎች ሸቀጦችን በመግዛት በተመጣጣኝ ዋጋ የሚያቀርብ ኢንተርፕራይዝ እንዲቋቋም ውሳኔ ላይ ተደርሶአል፡፡</p>
]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ginbot7.org/2013/04/29/%e1%8b%a8%e1%8c%a0%e1%88%9a%e1%8a%92%e1%88%b5%e1%89%b5%e1%88%ad-%e1%88%80%e1%8b%ad%e1%88%88%e1%88%9b%e1%88%ad%e1%8b%ab%e1%88%9d-%e1%8d%93%e1%88%ad%e1%88%8b%e1%88%9b-%e1%8b%89%e1%88%8e-%e1%8b%a8/feed/</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
		<item>
		<title>አዋሽ ወንዝ የሚሊዮኖችን ህይወት በእጁ እንደያዘ አደጋ ላይ መዉደቁ ተሳማ</title>
		<link>http://www.ginbot7.org/2013/04/29/%e1%8a%a0%e1%8b%8b%e1%88%bd-%e1%8b%88%e1%8a%95%e1%8b%9d-%e1%8b%a8%e1%88%9a%e1%88%8a%e1%8b%ae%e1%8a%96%e1%89%bd%e1%8a%95-%e1%88%85%e1%8b%ad%e1%8b%88%e1%89%b5-%e1%89%a0%e1%8a%a5%e1%8c%81-%e1%8a%a5/</link>
		<comments>http://www.ginbot7.org/2013/04/29/%e1%8a%a0%e1%8b%8b%e1%88%bd-%e1%8b%88%e1%8a%95%e1%8b%9d-%e1%8b%a8%e1%88%9a%e1%88%8a%e1%8b%ae%e1%8a%96%e1%89%bd%e1%8a%95-%e1%88%85%e1%8b%ad%e1%8b%88%e1%89%b5-%e1%89%a0%e1%8a%a5%e1%8c%81-%e1%8a%a5/#comments</comments>
		<pubDate>Mon, 29 Apr 2013 16:09:25 +0000</pubDate>
		<dc:creator>admin</dc:creator>
				<category><![CDATA[አማርኛ ዜናና መግለጫ]]></category>

		<guid isPermaLink="false">http://www.ginbot7.org/?p=5063</guid>
		<description><![CDATA[የብሉምበርግ ዜና ወኪል ሰራተኞችና አክስፐርቶች አዋሽ ወንዝና አካባቢዉን አጥንቶ ባወጣዉ ዜና መሰረት ወንዙንና አካባበዊን በተመለከተ እጅግ በጣም አስደንጋጭ ዜና ለአለምና ለኢትዮጵያ ህዝብ ማሰማቱ ከሰሞኑ ተሰማ። በስምጥ ሸለቆ ውስጥ የሚገኘው የበሰቃ ሀይቅ በመስኖ ስራዎች እና በተፈጥሮ እንቅስቃሴ ምክንያት ጨዋማነቱ በ15 እጥፍ በመጨመሩና በየአመቱ በክረምቱ ወራት ዝናብ በዘነበ ቁጥር ሀይቁ ወደ አዋሽ ወንዝ መፍሰስ ስለሚጀምር ይህ አደገኛ [...]]]></description>
			<content:encoded><![CDATA[<p>የብሉምበርግ ዜና ወኪል  ሰራተኞችና አክስፐርቶች አዋሽ ወንዝና አካባቢዉን አጥንቶ ባወጣዉ ዜና መሰረት ወንዙንና አካባበዊን በተመለከተ እጅግ በጣም አስደንጋጭ ዜና ለአለምና ለኢትዮጵያ ህዝብ ማሰማቱ ከሰሞኑ ተሰማ። በስምጥ ሸለቆ ውስጥ የሚገኘው የበሰቃ ሀይቅ በመስኖ ስራዎች እና በተፈጥሮ እንቅስቃሴ ምክንያት ጨዋማነቱ በ15 እጥፍ በመጨመሩና በየአመቱ በክረምቱ ወራት ዝናብ በዘነበ ቁጥር ሀይቁ ወደ አዋሽ ወንዝ መፍሰስ ስለሚጀምር ይህ አደገኛ አዝማሚያ ከአሁኑ ፈጣኝ እርምጃ ካልተወሰደ ወንዙን ለመጨረሻ ጊዜ ከጥቅም ውጭ ያደርገዋል የሚል ከፍተኛ ፍራቻ እንዳለ ለማወቅ ተችሏል።</p>
<p>ይህ በ1960ዎቹ 3 ስኼር ኪሎ ሜትር ብቻ የነበረዉ የበሰቃ ሐይቅ ዛሬ ከ45 ስኼር ኪሎሜትር በላይ መድረሱ በኤክስፐርቶቹ ተጠንቶ የተደረሰበት ሲሆን ሀይቁ ከልማት ስራ ጋር በተያያዘ በተፈጠረ የአፈር መሸርሸርና በመሬት የውስጥ እንቅስቃሴ ምክንያት ጨዋማነቱ ከመጠን በላይ እየጨመረ በመሄዱ የሚሊዮኖችን ህይወት ለአደጋ አጋልጧል።</p>
<p>የወያኔ የውሀና ኤነርጂ ሚኒስቴር የከርሰ ምድር ውሀዎች ዋና ሀላፊ የሆነዉ አቶ ተስፋ ታደሰ በግልጽ እንደተናገረዉ “ሀይቁ በራሱ ጊዜ ወደ አዋሽ መፍሰስ ከጀመረ የአዋሽ ወንዝ ለዘላለሙ ከጥቅም ውጭ ይሆናል” ብሏል። በሌላ በኩል ደግሞ የላይኛው አዋሽ ወንዝ የውሀ ጥናት ባለሙያ የሆነዉ አቶ  እንደሻው ታደሰ  ደግሞ የሰኔ ዝናብ ከመዝነቡ በፊት ሀይቁ ወደ አዋሽ ወንዝ እንዳይፈስ ወሳኝ ጥረት መደረግ አለበት ሲሉ አሳስበዋል። ባለሙያው እንደሚሉት ከአዲስ አበባ በስተምስራቅ የሚገኘው ሀይቅ ወደ ወንዙ ከፈሰሰ ከተሞችን ከማጥለቅለቅ አልፎ የአካባቢውን አርብቶ አደሮች ሊያፈናቅላቸው ይችላል።</p>
<p>ብሉምበርግ ሰፋ ባለዉ ጥናታዊ ዘገባዉ እንገለጸዉ የወያኔ አገዛዝ ላለፉት 14 አመታት የውሀ ፓምፖችን በመጠቀምና ቦዮችን በመስራት በሰቃን ለመቆጣጠር ጥረት ቢያደርግም አልተሰካላትም። በአለማያ ዩኒቨርስቲ የሲቪል የኢንጂነርግ ዲፓርትመንት አስተማሪ የሆኑት ፕሮፌሰር መገርሳ ዲንቃ እንደተናገሩት በአካባቢው የሚደረገው የመስኖ ስራ  ችግሩን አባብሶታል። ፕሮፌሰሩ የመሬት እንቅስቃሴው ለሀይቁ መስፋፋት ተጨማሪ አስተዋጽኦ አድርጎ ሊሆን እንደሚችልም ገልጸዋል። ሀኖም ስህተታቸዉንና ጥፋታቸዉን በተቃዋሚዎች ላይ ወይም ባለፉት መንግስታት ላይ ብቻ ማላከክ የሚቀናቸዉ የወያኔ ባለስልጣናት ከዚህ ቀደም በላይኛው አዋሽ ላይ ሲካሄድ የነበረው የመስኖ እንቅስቃሴ ችግሩን እንዳባባሰው ለማመን ባይፈልጉም በሁኔታዎች ተግድደዉ የችግሩን ስፋትና ጥልቀት አለማመን ተገደዋል።</p>
]]></content:encoded>
			<wfw:commentRss>http://www.ginbot7.org/2013/04/29/%e1%8a%a0%e1%8b%8b%e1%88%bd-%e1%8b%88%e1%8a%95%e1%8b%9d-%e1%8b%a8%e1%88%9a%e1%88%8a%e1%8b%ae%e1%8a%96%e1%89%bd%e1%8a%95-%e1%88%85%e1%8b%ad%e1%8b%88%e1%89%b5-%e1%89%a0%e1%8a%a5%e1%8c%81-%e1%8a%a5/feed/</wfw:commentRss>
		<slash:comments>0</slash:comments>
		</item>
	</channel>
</rss>
